28
ማህሌት ፋሲል ናፍቆት ዮሴፍ ሰላም ገረመው አለማየሁ አንበሴ ቅፅ 13 ቁጥር 718 ቅዳሜ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ብር 8.00 ነፃ አስተያየት ገፅ 3 ገፅ 5 ገፅ 8 ጥበብ ገፅ 20 መአህድ ወደ ገፅ 2 ዞሯል ረብሻ ወደ ገፅ 22 ዞሯል ቴዲ ወደ ገፅ 2 ዞሯል ጥቃት ወደ ገፅ 3 ዞሯል ገቢዎች ወደ ገፅ 4 ዞሯል ንግድና ኢኮኖሚ ገፅ 16 ፎቶ አንተነህ አክሊሉ በላይአብ ሞተርስ ለሁሉም ሰው መኪና ለማዳረስ አቅዷል አልሸባብ የፍንዳታ ጥቃት ለማድረስ ዝቷል የአሜሪካ ኤምባሲ ዜጐቹ ራሳቸውን ከጥቃት እንዲከላከሉ አስጠነቀቀ በከባድ የሙስና ወንጀል በተከሰሱት የቀድሞ የገቢዎችና ጉምሩክ መስሪያ ቤት የተለያዩ ሃላፊዎች እና ሠራተኞች እንዲሁም ታዋቂ ባለሃብቶች ላይ በፌደራል የስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቤ ህግ የቀረበው ክስ፣ ልደታ በሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞ ኤርፖርት ጉምሩክ ሃላፊ በዋስ ተለቀዋል በእነ አቶ መላኩ ፈንታ ላይ የቀረበው ክስ ሠኞ እና ማክሰኞ ይሰማል የገቢዎችና ጉምሩክ ተከሳሾች ክስ መሰማት ጀመረ 15ኛ ወንጀል ችሎት መሠማት የጀመረ ሲሆን በባለሀብቱ አቶ ማሞ ኪሮስ እና በገቢዎች ጉምሩክ ባለስልጣን የቦሌ አየር ማረፊያ ጉምሩክ የፍተሻ የስራ ሂደት መሪ በነበሩት በአቶ ዮሴፍ አዳዩ ላይ የቀረበው ክስ ከትናንት በስቲያ በዋለው ችሎት በንባብ ተሰምቷል፡፡ የመላው አማራ ህዝብ (መዐህድ) በአማራ ተወላጅ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው መፈናቀል በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ፡፡ መአህድ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ የአማራ ተወላጆችን መዐሕድ “የአማራ ተወላጅ ተማሪዎች መፈናቀል” እንዲቆም ጠየቀ መፈናቀል በተመለከተ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ማሳወቁንና መፈናቀሉ እንዲቆም መጠየቁን ጠቁሞ፤ ጉዳዩ እስካሁን እልባት አለማግኘቱን ገልጿል፡፡ በ15 ቀን ውስጥ ከወልቃይት ጠገዴ ሁለት ሺ ተማሪዎች ተፈናቅለዋል” ቴዲ አፍሮ በማርፈዱ ሸራተን እንዳይገባ ተከለከለ ሰሸዋንዳኝ የአልበም ምርቃት የተጋበዙት ሠራዊት ፍቅሬና ሰይፉ ፋንታሁንም ተከልክለዋል በኢትዮጵያ እና በናይጄሪያ የእግር ኳስ ጨዋታ በጋምቤላ ክልል ኚኝኛግ ወረዳ በደጋፊዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት የወረዳው አፈጉባኤ እና ወታደሮች እንደሞቱ ምንጮቻችን ገለፁ። የደቡብ ሱዳን አዋሳኝ በሆነችው የኚኝኛግ ወረዳ ባለፈው እሁድ ኢትዮጵያና ናይጄሪያ በአዲስ አበባ ስቴዲየም ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ባደረጉት ጨዋታ፣ የናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድን በማሸነፉ ደስታቸውን በጭፈራ በመግለጽ ላይ በነበሩ እና በድርጊቱ በተቆጡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በኢትዮጵያና ናይጄሪያ ጨዋታ ሰበብ የወረዳ አፈ- ጉባኤና ወታደሮች ሞቱ ደጋፊዎች መካከል ግጭት ተፈጥሮ የኚኝኛግ ወረዳ አፈጉባኤና ከሁለት በላይ ወታደሮች እንደሞቱ ታውቋል፡፡ ችግሩ እንደተፈጠረ ከፌደራልና ከክልል የተውጣጡ ባለስልጣናት ቦታው ድረስ በመሄድ የማረጋጋት ስራ መሥራታቸውን ምንጮቻችን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የክልሉ ፕሬዝዳንት ሁኔታው ለማየት ወደ ስፍራው የሄዱ ሲሆን ስለ ጉዳዩ ፕሬዝዳንቱን በስልክ ለመጠየቅ ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም፡፡ በሸራተን አዲስ ጋዝ ላይት ክለብ ከትናንት በስቲያ ሰተካሄደው የድምፃዊ ሸዋንዳኝ ኃይሉ “ስጦታሽ” አልበም ምርቃት በክብር እንግድነት የተጠራው ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፤ ሰዓት አርፍዶ በመድረሱ እንዳይገባ ተከልክሎ ከበር ተመለሰ፡፡ ቴዲ አፍሮ ከምሽቱ 5፡30 ላይ የምርቃት ስነስርዓቱ ወደሚካሄድበት ጋዝ ላይት ክለብ ሊገባ ሲል የጥበቃ ሰራተኞች “ጥሪው 4 ሰዓት እንጂ 5፡30 ሰዓት አይደለም” በማለት እንዳይገባ እንደከለከሉት ለማወቅ ተችሏል። አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬና ሰይፉ ፋንታሁንን ጨምሮ በርካታ ያረፈዱ እንግዶች ወደ ጋዝ ላይት ክለብ እንዳይገቡ መከልከላቸውን የዓይን እማኞች ገልፀዋል፡፡ ሸዋንዳኝ፤ ቴዲ አፍሮ እንዳይገባ መከልከሉን የሰማው መድረክ ላይ ሆኖ እንደሆነ የገለፁት ምንጮች፤ በዚህም ማዘኑን ተናግረዋል። አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች፤ ሁለቱ እንዳላቸው ዜጎችን እያቀጨጨ የሚፈረጥም መንግስት… ብዙ አይራመድም ስንት እድሜ ይኖረዋል? ዲሞክራሲያችን በስንት ዲጂት እንዳደገ ይነገረን! ልጆቻቸውና ሚስቶቻቸው አረብ አገር የጠፉባቸው ቤተሰቦች ኤጀንሲዎችንና መንግስትን አማረሩ ኢትዮጵያዊው ሠዓሊ በአሜሪካ፤ ጃክሰን ጐዳና ትግራይ ክልል የማይአይኒ በተባለ ስፍራ የሚገኝ የኤርትራ ስደተኞች ካምፕ ውስጥ በተቀሰቀሰ ረብሻ የአንድ ሠው ህይወት ከጠፋ በኋላ፣ ተጠያቂ ናቸው የተባሉ ሰዎች እንደታሰሩ ምንጮቻችን አመለከቱ፡፡ ስደተኞች የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን በመቃወም ቢሮዎች የሰባበሩ ሲሆን፣ ወደ ጎንደር የሚወስደውም መንገድ በኤርትራ የስደተኞች ካምፕ ረብሻ ተቀሰቀሰ የአንድ ሰው ህይወት አልፏል ባለፈው እሁድ በቦሌ ሚካኤል አካባቢ ከደረሰው ፍንዳታ ጋር ተያይዞ ሁለት ተጨማሪ የፍንዳታ ጥቃት ለማድረስ አልሸባብ የተሰኘው የሶማሊያ ቡድን እንደዛተ የገለፀው የአሜሪካ ኤምባሲ፤ የዛቻው ተአማኒነት ባይረጋገጥም በኢትዮጵያ የሚገኙ አሜሪካዊያን ጥንቃቄ እንዳይለያቸው አሳሰበ፡፡ የኢትዮጵያና የናይጄሪያ ቡድኖች ግጥሚያ በሚካሄድበት ሰዓት ጥቃት ለመፈፀም ሲዘጋጁ የነበሩ ሁለት ሰዎች መሞታቸው የሚታወስ ሲሆን በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት በማወጅና ሽብር ለመፈፀም በመዛት የሚታወቀው አልሸባብ “ድርጊቱ በኔ አባላት የተፈፀመ ነው” ብሏል፡፡ አልሸባብ በቦሌ ሚካኤል ለተከሰተው ፍንዳታ ሃላፊነት እንደሚወስድ በትዊተር እንዳስታወቀ ኤምባሲው ጠቅሶ ባሰራጨው ማሳሰቢያ፤ በፒያሳና በቸርችል ጐዳና አካባቢ የፍንዳታ ጥቃት ለመፈፀም እንደዛተም ገልጿል፡፡ በቦሌ ሚካኤል በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተከሰተው ፍንዳታ ሁለት የሶማሊያ ተወላጆች መሞታቸውን የገለፀው ፖሊስ፤ ከሟቾቹ አንዱ የኢትዮጵያ ማሊያ በመልበስ ከኳስ ተመልካቾች መሃል የፍንዳታ ጥቃት ለመፈፀም እየተዘጋጀ እንደነበር ጠቁሟል፡፡ ለጥቃት የታሰበው ፈንጂ እዚያው ፈንድቶ ነው ሁለቱ አሸባሪዎች የሞቱት

Issue 718

Embed Size (px)

DESCRIPTION

news Amharic

Citation preview

Page 1: Issue 718

ማህሌት ፋሲል

ናፍቆት ዮሴፍ

ሰላም ገረመው

አለማየሁ አንበሴ

ቅፅ 13 ቁጥር 718 ቅዳሜ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ብር 8.00

ነፃ አስተያየት ገፅ 3

ገፅ 5 ገፅ 8

ጥበብ ገፅ 20

መአህድ ወደ ገፅ 2 ዞሯል ረብሻ ወደ ገፅ 22 ዞሯል

ቴዲ ወደ ገፅ 2 ዞሯል

ጥቃት ወደ ገፅ 3 ዞሯል

ገቢዎች ወደ ገፅ 4 ዞሯል

ንግድና ኢኮኖሚ ገፅ 16

ፎቶ

አን

ተነህ

አክ

ሊሉ

በላይአብ ሞተርስ ለሁሉም ሰው መኪና ለማዳረስ አቅዷል

አልሸባብ የፍንዳታ ጥቃት ለማድረስ ዝቷል

የአሜሪካ ኤምባሲ ዜጐቹ ራሳቸውን ከጥቃት እንዲከላከሉ አስጠነቀቀ

በከባድ የሙስና ወንጀል በተከሰሱት የቀድሞ የገቢዎችና ጉምሩክ መስሪያ ቤት የተለያዩ ሃላፊዎች እና ሠራተኞች እንዲሁም ታዋቂ ባለሃብቶች ላይ በፌደራል የስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቤ ህግ የቀረበው ክስ፣ ልደታ በሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት

• የቀድሞ ኤርፖርት ጉምሩክ ሃላፊ በዋስ ተለቀዋል • በእነ አቶ መላኩ ፈንታ ላይ የቀረበው ክስ ሠኞ እና ማክሰኞ ይሰማል

የገቢዎችና ጉምሩክ

ተከሳሾች ክስ መሰማት ጀመረ

15ኛ ወንጀል ችሎት መሠማት የጀመረ ሲሆን በባለሀብቱ አቶ ማሞ ኪሮስ እና በገቢዎች ጉምሩክ ባለስልጣን የቦሌ አየር ማረፊያ ጉምሩክ የፍተሻ የስራ ሂደት መሪ በነበሩት በአቶ ዮሴፍ አዳዩ ላይ የቀረበው ክስ ከትናንት በስቲያ በዋለው ችሎት በንባብ ተሰምቷል፡፡

የመላው አማራ ህዝብ (መዐህድ) በአማራ ተወላጅ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው መፈናቀል በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ፡፡ መአህድ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ የአማራ ተወላጆችን

መዐሕድ “የአማራ ተወላጅ ተማሪዎች መፈናቀል” እንዲቆም ጠየቀ

መፈናቀል በተመለከተ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ማሳወቁንና መፈናቀሉ እንዲቆም መጠየቁን ጠቁሞ፤ ጉዳዩ እስካሁን እልባት አለማግኘቱን ገልጿል፡፡

በ15 ቀን ውስጥ ከወልቃይት ጠገዴ ሁለት ሺ ተማሪዎች ተፈናቅለዋል”

ቴዲ አፍሮ በማርፈዱ ሸራተን እንዳይገባ ተከለከለሰሸዋንዳኝ የአልበም ምርቃት የተጋበዙት ሠራዊት

ፍቅሬና ሰይፉ ፋንታሁንም ተከልክለዋል

በኢትዮጵያ እና በናይጄሪያ የእግር ኳስ ጨዋታ በጋምቤላ ክልል ኚኝኛግ ወረዳ በደጋፊዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት የወረዳው አፈጉባኤ እና ወታደሮች እንደሞቱ ምንጮቻችን ገለፁ።

የደቡብ ሱዳን አዋሳኝ በሆነችው የኚኝኛግ ወረዳ ባለፈው እሁድ ኢትዮጵያና ናይጄሪያ በአዲስ አበባ ስቴዲየም ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ባደረጉት ጨዋታ፣ የናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድን በማሸነፉ ደስታቸውን በጭፈራ በመግለጽ ላይ በነበሩ እና በድርጊቱ በተቆጡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

በኢትዮጵያና ናይጄሪያ ጨዋታ ሰበብ የወረዳ አፈ-ጉባኤና ወታደሮች ሞቱ

ደጋፊዎች መካከል ግጭት ተፈጥሮ የኚኝኛግ ወረዳ አፈጉባኤና ከሁለት በላይ ወታደሮች እንደሞቱ ታውቋል፡፡

ችግሩ እንደተፈጠረ ከፌደራልና ከክልል የተውጣጡ ባለስልጣናት ቦታው ድረስ በመሄድ የማረጋጋት ስራ መሥራታቸውን ምንጮቻችን ጨምረው ገልፀዋል፡፡

የክልሉ ፕሬዝዳንት ሁኔታው ለማየት ወደ ስፍራው የሄዱ ሲሆን ስለ ጉዳዩ ፕሬዝዳንቱን በስልክ ለመጠየቅ ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም፡፡

በሸራተን አዲስ ጋዝ ላይት ክለብ ከትናንት በስቲያ ሰተካሄደው የድምፃዊ ሸዋንዳኝ ኃይሉ “ስጦታሽ” አልበም ምርቃት በክብር እንግድነት የተጠራው ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፤ ሰዓት አርፍዶ በመድረሱ እንዳይገባ ተከልክሎ ከበር ተመለሰ፡፡

ቴዲ አፍሮ ከምሽቱ 5፡30 ላይ የምርቃት ስነስርዓቱ ወደሚካሄድበት ጋዝ ላይት ክለብ ሊገባ ሲል የጥበቃ ሰራተኞች “ጥሪው 4 ሰዓት እንጂ

5፡30 ሰዓት አይደለም” በማለት እንዳይገባ እንደከለከሉት ለማወቅ ተችሏል። አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬና ሰይፉ ፋንታሁንን ጨምሮ በርካታ ያረፈዱ እንግዶች ወደ ጋዝ ላይት ክለብ እንዳይገቡ መከልከላቸውን የዓይን እማኞች ገልፀዋል፡፡ ሸዋንዳኝ፤ ቴዲ አፍሮ እንዳይገባ መከልከሉን የሰማው መድረክ ላይ ሆኖ እንደሆነ የገለፁት ምንጮች፤ በዚህም ማዘኑን ተናግረዋል። አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች፤ ሁለቱ እንዳላቸው

ዜጎችን እያቀጨጨ የሚፈረጥም

መንግስት… ብዙ አይራመድም ስንት

እድሜ ይኖረዋል?

ዲሞክራሲያችን በስንት

ዲጂት እንዳደገ ይነገረን!

ልጆቻቸውና ሚስቶቻቸው አረብ አገር የጠፉባቸው

ቤተሰቦች ኤጀንሲዎችንና

መንግስትን አማረሩ

ኢትዮጵያዊው ሠዓሊ በአሜሪካ፤ ጃክሰን ጐዳና

ትግራይ ክልል የማይአይኒ በተባለ ስፍራ የሚገኝ የኤርትራ ስደተኞች ካምፕ ውስጥ በተቀሰቀሰ ረብሻ የአንድ ሠው ህይወት ከጠፋ በኋላ፣ ተጠያቂ ናቸው የተባሉ ሰዎች እንደታሰሩ ምንጮቻችን አመለከቱ፡፡ ስደተኞች የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን በመቃወም ቢሮዎች የሰባበሩ ሲሆን፣ ወደ ጎንደር የሚወስደውም መንገድ

በኤርትራ የስደተኞች ካምፕ ረብሻ ተቀሰቀሰ

የአንድ ሰው ህይወት አልፏል

ባለፈው እሁድ በቦሌ ሚካኤል አካባቢ ከደረሰው ፍንዳታ ጋር ተያይዞ ሁለት ተጨማሪ የፍንዳታ ጥቃት ለማድረስ አልሸባብ የተሰኘው የሶማሊያ ቡድን እንደዛተ የገለፀው የአሜሪካ ኤምባሲ፤ የዛቻው ተአማኒነት ባይረጋገጥም በኢትዮጵያ የሚገኙ

አሜሪካዊያን ጥንቃቄ እንዳይለያቸው አሳሰበ፡፡

የኢትዮጵያና የናይጄሪያ ቡድኖች ግጥሚያ በሚካሄድበት ሰዓት ጥቃት ለመፈፀም ሲዘጋጁ የነበሩ ሁለት ሰዎች መሞታቸው የሚታወስ ሲሆን በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት በማወጅና ሽብር ለመፈፀም በመዛት የሚታወቀው አልሸባብ “ድርጊቱ በኔ አባላት የተፈፀመ

ነው” ብሏል፡፡ አልሸባብ በቦሌ ሚካኤል ለተከሰተው

ፍንዳታ ሃላፊነት እንደሚወስድ በትዊተር እንዳስታወቀ ኤምባሲው ጠቅሶ ባሰራጨው ማሳሰቢያ፤ በፒያሳና በቸርችል ጐዳና አካባቢ የፍንዳታ ጥቃት ለመፈፀም እንደዛተም ገልጿል፡፡

በቦሌ ሚካኤል በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተከሰተው ፍንዳታ ሁለት

የሶማሊያ ተወላጆች መሞታቸውን የገለፀው ፖሊስ፤ ከሟቾቹ አንዱ የኢትዮጵያ ማሊያ በመልበስ ከኳስ ተመልካቾች መሃል የፍንዳታ ጥቃት ለመፈፀም እየተዘጋጀ እንደነበር ጠቁሟል፡፡

ለጥቃት የታሰበው ፈንጂ እዚያው ፈንድቶ ነው ሁለቱ አሸባሪዎች የሞቱት

Page 2: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 2 ዜና

መልካሙ ተክሌ

አለማየሁ አንበሴ

አለማየሁ አንበሴ

አለማየሁ አንበሴ

ተመራቂዎች ወደ ገፅ 4 ዞሯል

በቅርቡ “ኢንተርናሽናል ስታር ፎር ኳሊቲ” የሚል ሽልማት የተሸለመው ኔክስት ዲዛይኒንግ ኢንስቲትዩት ከሌሎች ሀገራት በተለይም ከአፍሪካ ሀገራት የዲዛይኒንግ ተማሪዎች ተቀብዬ ለማስተማር አቅጃለሁ አለ፡፡ ሽልማቱ ዓለም አቀፍ ዕውቅናዬን ይጨምርልኛል ብሏል-ተቋሙ፡፡

ኔክስት ዲዛይኒንግ ኢንስቲትዩት በ1996 ዓ.ም ማስተማር የጀመረ ሲሆን በልብስ ቅድ፣ በልብስ ስፌት፣ በፋሽን እና በተያያዥ ሙያዎች በኮሌጅ ደረጃ እያስተማረ ይገኛል፡፡ ጄኔቭ የሚገኘው ቢድ ቢዝነስ ኢኒሸቲቭ፤ ኔክስት ዲዛይኒንግን የሸለመው ሰባት የጥራት መመዘኛ መርሆዎችን መመዘኛ አድርጐ ሲሆን ከነዚህም አንዱ የደንበኛን ፍላጐት እና ግምት ማርካት ነው፡፡ በርካታ የፋሽን ትርዒቶች በማቅረብም የሚታወቀው ኔክስት ዲዛይኒንግ፤ ተመራቂ ተማሪዎቹን እያወዳደረ ለአጫጭር ኮርስ ሕንድ የሚልክ ሲሆን ገንዘብ ከፍለው መማር ላልቻሉ ወገኖችም የነፃ ትምሕርት ዕድል በማመቻቸት 165 ተማሪዎች እንዳስመረቀ ከኮሌጁ የወጣው መግለጫ ያመለክታል፡፡

የትምህርት ቤቱ ባለቤት እና ሥራ አስኪያጅ ሞዴልና ዲዛይነር ወ/ሮ ሳራ መሐመድ ኦስማን በቅርቡ መሸለማቸውን አስመልክቶ “ሽልማቱ በማበረታታት ለውጥ እንድናመጣ ያደርጋል። ከሌላው ዓለም ጋርም ተወዳዳሪ ያደርገናል። ከኢትዮጵያ ውጪ ተማሪዎች እንድንቀበል ያስችለናል፡፡” ብለዋል፡፡

“ኔክስት ዲዛይኒንግ” ከሌሎች ሀገራት ተማሪ

ለመቀበል አስቧል

በሽብር ወንጀል የ14 ዓመት እስር ተፈርዶበት በማረሚያ ቤት የሚገኘው የቀድሞው የ“አውራምባ ታይምስ” ጋዜጣ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ባደረገው ሲኤንኤን “መልቲ ቾይዝ” የሽልማት ድርጅት ተሸለመ፡፡

ጋዜጠኛው ሽልማቱን ያሸነፈው በአፍሪካ የነፃ ፕሬስ ዘርፍ ሲሆን ደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የሽልማት ስነ ስርአት ከአስራ አንድ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 27 ጋዜጠኞች በተለያዩ ዘርፎች እንደተሸለሙ ታውቋል፡፡

ጋዜጠኛው በእስር ላይ በመሆኑ ባለቤቱ ብርሃን ተስፋዬ እና ልጁ ፍትህ ውብሸት በስፍራው ተገኝተው ሽልማቱን ተቀብለዋል፡፡ ውብሸት በተወዳዳሪነት በቀረበበት ዘርፍ ከፍተኛ ፉክክር እንደነበር የሽልማቱ አዘጋጆች ገልፀው፤ ጋዜጠኛው በ“አውራምባ ታይምስ” ጋዜጣ ላይ በሚሰራበት ወቅት በፀረ - ሽብር ህጉ ተከሶ የ14 አመት እስራት እንደተፈረደበት አስታውሰው፤ ለነፃ ፕሬስ መጐልበት በከፈለው መስዋዕትነት ለሽልማት መመረጡን ጠቁመዋል፡፡

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ የ“ሲ ኤን ኤን መልቲ ቾይዝ” ተሸላሚ ሆነ

ከጐንደር ዩኒቨርስቲ በ“ልማትና የአካባቢ እንክብካቤ ጥናት” የተመረቁ ተማሪዎች በመንግስትም ይሁን በግል መስሪያ ቤቶች የስራ መደብ ዝርዝር ውስጥ ባልተካተተ የትምህርት ዘርፍ በመመረቃችን ስራ አጥ ሆነናል ሲሉ አማረሩ። የትምህርት ክፍሉ ሃላፊዎች በበኩላቸው፤ ከፌደራልና ከክልል ሲቪል ሠርቪስ መስሪያ ቤቶች ጋር ተነጋግረን ችግሩን ለመፍታት ጥረት እያደረግን ነው፤ ጥቂት የማይባሉ ተመራቂዎችም ስራ ማግኘት ጀምረዋል ብለዋል፡፡

በ2003 ዓ.ም ከትምህርት ክፍሉ በመጀመሪያ ዲግሪ መመረቃቸውን የሚገልፁት ክብሮም ሃጐስና ጓደኞቹ፤ በትምህርት ክፍሉ ሲመደቡ ጀምሮ ስራ የመቀጠር ዕድል እንደሌላቸው እያወቁ ምርጫ በማጣት ትምህርቱን ለመማር መገደዳቸውን ያስታውሳሉ፡፡ በሶስት አመታት ቆይታቸው ዲፓርትመንቱ በግለሠቦች ይሁንታ መጀመሩን በሚገልፅ መልኩ “የሙሉቀን ልጆች” እየተባሉ ይጠሩ እንደነበር የገለፁት እነ ክብሮም፤ በትምህርት አሠጣጡ ላይ ቅሬታ ያለው ተማሪ ባይኖርም ለአመታት በደከሙበት የትምህርት መስክ ከተመረቁ በኋላ ስራ ማጣታቸው በርካቶችን ተስፋ እንዳስቆረጠ ተናግረዋል፡፡ “በግሌም ሆነ የተማሪዎቹን ጥያቄ ይዤ ለበርካታ ጊዜያት የፌደራል ሲቪል ሠርቪስ

• “የተመረቃችሁበት የትምህርት መስክ አይታወቅም” - ቀጣሪዎች• “በስራ አጥነት ተመዝግባችሁ ተደራጁ” ተብለዋል

• ዩኒቨርሲቲው በዘረፉ ማስተማሩን ቀጥሏል

የጐንደር ዩኒቨርስቲ የ“ልማትና አካባቢ እንክብካቤ” ተመራቂዎች የሚቀጥረን አጣን አሉ

ሚኒስቴር ድረስ በመመላለስ በትምህርት መስኩ የስራ እድሎች እንዲፈጠሩ ለመጠየቅ ሞክሬያለሁ” የሚለው ክብሮም፤ እስከዛሬ ግን ምላሽ አለማግኘቱን ገልጿል፡፡

በሃገሪቱ በሚወጡ የስራ ማስታወቂያዎች “በልማትና የአካባቢ እንክብካቤ የትምህርት ዘርፍ የተመረቀ” የሚል የስራ መደብ ማስታወቂያ እስከዛሬ ወጥቶ አያውቅም ያለው ተማሪው፤ በ2004 ዓ.ም የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር በ“ዴቨሎፕመንታል ስተዲስ” የትምህርት መስክ ማስታወቂያ ሲያወጣ ተያያዥነት አለው በሚል ለመመዝገብ ሄደው እንደነበር አስታውሶ፣ “የተመረቃችሁበት የትምህርት መስክ አይታወቅም” ተብለው ማስረጃቸው እንደተመለሰላቸው ገልጿል።

የስራ እድሉን ለማግኘት በአዲስ አበባ ከተማ 114 ወረዳዎች እየዞረ ከቀጣሪ አካላት ጋር መነጋገሩን የሚገልፀው ክብሮም፤ ሁሉም ግን ለትምህርት መስኩ የሚሆን የስራ መደብ እንደሌላቸው መረዳቱን ተናግሯል፡፡ እንደውም በሚኖርበት የካ ክፍለ ከተማ፣ የክፍለ ከተማውን አስተዳደር ባነጋገረበት ወቅት “ለምን በስራ አጥነት ተመዝግባችሁ አትደራጁም” የሚል ምላሽ እንደተሠጠው ገልጿል።

“ከተመረቅንበት ጊዜ ጀምሮ በየእለቱ የሚወጡ የስራ ማስታወቂያዎችን ከጓደኞቼ ጋር ሆነን አንድም ቀን ሣናሣልፍ ስንከታተል ቆይተናል”

የሚለው ተማሪው፤ “ተያያዥ ለሆኑ የስራ መስኮች የትምህርት ማስረጃ ስናስገባ በመጀመሪያ አካባቢ ‘ይሄ የትምህርት መስክ አይታወቅም’ እየተባልን ማመልከቻችን ተመላሽ ይደረግ ነበር፤ እየቆየ ግን ማመልከቻችንን ይቀበሉንና በኋላ ያስወጡናል” ብሏል፡፡ በዚህም ምክንያት “የቤተሠቦቻችንን ሃብት አባክነን፣ ተምረን እንዳልተማርን ሆነን መና ቀርተናል” የሚለው ክብሮም፤ በግለሠቦች በጐ ፈቃድ እንደተጀመረ የሚነገርለት የትምህርት ክፍሉ ግን ዛሬም ተማሪዎችን እየተቀበለ ማስተማሩንና ማስመረቁን እንደቀጠለ ገልጿል፡፡

“ልማትና የአካባቢ እንክብካቤ ጥናት” የተባለው የትምህርት መስክ በጐንደር ዩኒቨርስቲ ብቻ እንደሚሠጥና በ1999 ዓ.ም እንደተጀመረ የሚናገሩት ተማሪዎቹ፤ ከ2003 ቀደም ብሎ የተመረቁትም ሆኑ ከዚያ በኋላ የተመረቁት አብዛኞቹ ተማሪዎች ስራ አጥ እንደሆኑ ይገልፃሉ፡፡ አንዳንዶቹም ከትምህርት መስኩ ውጭ ባሉ ስራዎች መሠማራታቸውን ተናግረዋል፡፡

ወደ ትምህርት ክፍሉ ተመድበው በገቡበት ወቅት በተሠጣቸው ማብራሪያ ላይ ከሴቶችና ህፃናት ጉዳይ፣ ከቱሪዝም፣ ከአካባቢ ጥበቃ፣ ከስርአተ ፆታ እንዲሁም ከፖሊሲ ቀረፃ ጋር በተገናኙ የስራ መስኮች ሠፊ የስራ እድል አላችሁ ተብሎ ተነግሮናል ያሉት ተመራቂዎቹ፤ ሆኖም የተባሉት የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ጀርባቸውን እንደሰጧቸው ይናገራሉ፡፡

የትምህርት ክፍሉ ተጠሪ የነበሩትን አቶ ሲሣይ

ከሃያ አራት አመታት በፊት በይዞታነት የያዝነውና ንብረት ያፈራንበት መኖሪያ ቦታችን ለ40/60 የቤት ፕሮግራም ግንባታ ይፈለጋል በሚል ተገቢው ካሣና ምትክ ቦታ ሳይሰጠን ተነሱ ተባልን ሲሉ የቦሌ ቡልቡላ ወረዳ 12 ቀጠና 5 ነዋሪዎች ቅሬታ አቀረቡ፡፡

ከ40 በላይ የሆኑት እነዚህ ቅሬታ አቅራቢዎች በቦታው ላይ ከ1982 ዓ.ም ጀምሮ መስፈራቸውን፣ ህጋዊ ነዋሪ ስለመሆናቸውም በተለያዩ ጊዜያት ወረዳው ከክፍለ ከተማው እንዲሁም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር የተፃፃፋቸው ደብዳቤዎችና ሰነዶች በእጃቸው እንዳለ ለአዲስ አድማስ ገልፀው፤ በ2005 ዓ.ም መጀመሪያ ቦታው ለ40/60 የቤቶች ግንባታ ስለሚፈለግ “ተነሺ ናችሁ” የሚል ማሳሰቢያ ከቦሌ ክ/ከተማ የመሬት ልማት ማኔጅመንት ጽ/ቤት በተደጋጋሚ እንደተላለፈላቸው አስታውቀዋል፡፡

በህጉ መሠረት ተገቢው ምትክ ቦታና ካሣ እስከተሰጣቸው ድረስ ቅሬታ እንደሌላቸው ለከተማ አስተዳደሩ ማሳወቃቸውን ቅሬታ አቅራቢዎቹ ገልፀው፤ ይሁን እንጂ የወረዳው አስተዳደሮች የአየር ካርታ ላይ ስለሌላችሁ ካሣና ምትክ ቦታ አይገባችሁም የሚል ምላሽ ሰጥተውናል ብለዋል። “እኛ በቦታው ላይ ህጋዊ ነዋሪ መሆናችንን የሚያረጋግጡ የተለያዩ ማስረጃዎች አሉን” የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ ግብር የከፈልንባቸውን፣ መብራት እና ውሃ ለማስገባት የተፃፃፍናቸውን ደብዳቤዎች እንዲሁም ወረዳው በተለያዩ ጊዜያት ለከተማ አስተዳደሩ ስለ ህጋዊነታችን የፃፋቸው ሰነዶችን በማስረጃነት

እየተገባ፣ የልማት ስራው እንዲቀጥል” የሚል ትዕዛዝ ተላልፏል የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ ይሄ ከፍተኛ ስጋት አሳድሮብናል ብለዋል፡፡ ጉዳዩ ትኩረት አግኝቶ እንዲጤንላቸውም ከሁለት ጊዜ በላይ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ መፃፋቸውንና ደብዳቤያቸው ምላሽ አለማግኘቱን የሚናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ “ህጋዊ መብታችን ተጥሶ ለአመታት ከኖርንበት ቦታ ያለ አግባብ ልንፈናቀል” ነው ሲሉ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

ተነሺዎቹ ባቀረቡት ቅሬታ ዙሪያ በስልክ አግኝተን ያነጋገርናቸው በቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 12 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፀባይ መሸሻ በሠጡን ምላሽ፤ ከ1982 እስከ 1997 ዓ.ም በቦታው በህጋዊነት ያሉት ቀደም ብሎ የወጣው መመሪያ በሚያዘው መሠረት ተገቢውን ካሣና ምትክ ቦታ እንዲያገኙ የሚያስችላቸውን ፎርም እየሞሉ መሆኑን አስታውቀው፣ ከ1997 ወዲህ ያሉት ግን መስተናገድ የሚችሉት በ2003 የተነሣ የአየር ካርታን መሠረት አድርጐ ነው ብለዋል፡፡ በዚህ ማዕቀፍ ለተካተቱት የካሣና የምትክ ቦታ አሠጣጥ ረቂቅ መመሪያ ገና እየወጣ መሆኑን ያመለከቱት ሃላፊው መመሪያው እስኪደርስ ድረስ የልማቱ ስራ መቆም ስለሌለበት ገና የሚወጣውን መመሪያ ታሣቢ ባደረገ መልኩ እንዲነሡ እናደርጋለን ብለዋል፡፡ “እኛም ለህዝቡ ጥቅም የቆምን ነን” ያሉት ሃላፊው፤ ለስራው ስኬታማነት ሲባልም ተነሺዎቹ ያላቸውን አጠቃላይ መረጃ በዝርዝር ያዙ በተባልነው መሠረት እየያዝን ነው ብለዋል፡፡

ከ40 በላይ ነዋሪዎች ተነሱ ተብለዋል

ለ40/60 ቤቶች ግንባታ የሚፈለገው ቦታ እያወዛገበ ነው

ብናቀርብም ተቀባይነት አጥተናል ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና

ማናጅመንት ጽ/ቤት መስከረም 16 ቀን 2006 ዓ.ም ለቦሌ ክ/ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽ/ቤት በፃፈው ደብዳቤ፤ “በቀጣይ ተግባራዊ በሚደረግ የደንብ ማስፈፀሚያ መመሪያ መሠረት፤ የተነሺ መብታቸውን ለወደፊት ታሳቢ ያደረገ ውል

ገቢዎች ከገፅ 1 የዞረመፈናቀሉ ሊቆም ቀርቶ ተጠናክሮ መቀጠሉንና

በቅርቡም ከጉራፈርዳ፣ ከቤኒሻንጉል እና ከወልቃይት ጠገዴ የአማራ ተወላጅ ተማሪዎች መፈናቀላቸውን የጠቆመው መዐህድ፤ ድርጊቱ በአገሪቱ ስርዓት አልበኝነት መንሰራፋቱን ያሳያል ብሏል፡፡

ከተማሪዎች በተጨማሪ የአማራ ተወላጅ አርሶ አደሮችንም ለይቶ ማፈናቀሉ ለመሪር ሀዘን እንደዳረገው መአህድ ገልፆ፤ አንድን ብሄር ማዕከል ያደረገ ማፈናቀል እንዲቆም ጠይቋል፡፡

ባለፉት 15 ቀናት ብቻ “አካባቢያችሁ አይደለም” በሚል ከወልቃይት ጠገዴ ሁለት

ሺህ ተማሪዎች መፈናቀላቸውን የገለፁት የመአህድ ፕሬዚዳንት አቶ ሸዋንግዛው ገብረስላሴ፤ ከጉራፈርዳም ተማሪዎች ተፈናቅለው ከትምህርት መስተጓጐላቸውንና ለጊዜው ቁጥራቸው በውል አለመታወቁን ፕሬዚዳንቱ ጨምረው ገልፀዋል፡፡ “ከጉራፈረዳ ምን ያህል ተማሪዎች እንደተፈናቀሉና በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ የሚያጣራ ቡድን ልከናል” ያሉት አቶ ሸዋንግዛው፤ አጣሪ ቡድኑ ሁኔታውን አጣርቶ ሲመለስ መዐህድ በድጋሚ የአቋም መግለጫ እንደሚያወጣም ተናግረዋል፡፡

“ተማሪዎች የወደፊት አገር ተረካቢ ሲሆኑ አርሶ አደሮችም የአገር ህልውና ምሰሶ ስለሆኑ በአገራቸው የትኛውም ቦታ የመማርና የመስራት መብታቸው

ተከብሮ፤ ተማሪዎችም ወደ ትምህርት፣ አርሶ አደሮችም ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ እንጠይቃለን” ብለዋል፤ ፕሬዚዳንቱ፡፡

የአማራ ተወላጆችን ከተለያዩ አካባቢዎች ከማፈናቀል በተጨማሪ የአማራውን ክልል ለማጥበብ ወደ አጐራባች ክልሎች የሚደረገው የመሬት ሽንሸና ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆም መዐህድ በመግለጫው የጠየቀ ሲሆን በአማራ ህልውና ላይ በተደጋጋሚ እየደረሰ ያለው ስልታዊ እንቅስቃሴ እና ትንኮሳ ሊገታ ይገባል ሲል አሳስቧል፡፡ ሌሎች ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪል ማህበራትም ይህንን ኢ-ሰብአዊ ድርጊትና መብት ረገጣ እንዲያወግዙ ጠይቋል፡፡

ቅርበት ቴዲ አፍሮ በፕሮግራሙ ላይ ቀድሞ መገኘት ነበረበት ብለዋል፡፡ ድምፃዊ ሸዋንዳኝን ስለ ጉዳዩ በስልክ ጠይቀነው፣ መልስ ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡

ከትላንት በስቲያ ምሽት በተካሄደው የምርቃት ስነ ስርዓት ላይ ሸዋንዳኝ ከአዲሱ አልበም አስር ዘፈኖችን የተጫወተ ሲሆን የተዘጋጀለትን አዲካ እና ኤም ጂ ፕሮሞሽን ያዘጋጁለቱንም ኬክ በዚያው ፕሮግራም ላይ ቆርሷል፡፡ ሸዋንዳኝና ቴዲ አፍሮ በአንድ የሙዚቃ ባንድ ውስጥ ለረጅም አመታት አብረው የሰሩ ሲሆን ቴዲ አፍሮ ሲያገባ ሸዋንዳኝ ሚዜው ነበር፡፡

ማርፈድ የስንፍና ምልክት መሆኑን የተናገረው አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ፤ሸራተን ስንደርስ የሆቴሉ ስራ አስኪያጅ በሩን ዘግተው እንደሄዱ ተነግሮናል ብሏል፡፡ “በሌሎች አገሮችም የተለመደ ነው፤ናይት ክለብ ከሞላ ሰው እስኪቀንስ መግባት አይቻልም” ያለው ሰራዊት፤ “እኛ ታዋቂ ስለሆንን ለምን ተከለከልን የሚል ቅሬታ አላደረብንም” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡

ቴዲ ከገፅ 1 የዞረ

Page 3: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 3

ናፍቆት ዮሴፍ

’í ›e}Á¾ƒ

በተለያዩ ኤጀንሲዎች በኩል በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ህጋዊ ውል ፈፅመው ወደተለያዩ የአረብ አገራት ለስራ የሄዱ እህቶቻችን፣

ልጆቻችን እና ሚስቶቻችን በችግር ላይ ሆነው አቤት የምንልበት አጥተናል ሲሉ የተጓዥ ቤተሰቦች አማረሩ፡፡ ኤጀንሲዎቹን ስንጠይቅ ምላሽ አይሰጡም፣ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይም በቀጠሮ እያመላለስን ጉዳያችን እልባት ሳያገኝ ለመኝታ፣ ለቀለብ፣ ለጊዜና ለጉልበት ብክነት ተዳርገናል ይላሉ፤ የተጓዥ ቤተሰቦች፡፡

ከአምቦ ከተማ የ5 ወር ህፃን ልጇን አዝላ የእህቷን ጉዳይ እልባት ለማግኘት የምትመላለሰው ፋጤ ኑሬ ራህመት ኑሪ ሞሳ እህቷ “ይጠቅለን” በተባለው ኤጀንሲ በኩል ወደ ሳውዲ ሄዳ ጉልበቷ ያለ ደሞዝ እየተበዘበዘ እንደሆነ ደውላ እንደነገረቻች ገልፃለች፡፡ “ህፃን ልጄን ይዤ አንዴ ወደ ኤጀንሲው፣ አንዴ ወደ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ስመላለስ ብቆይም ምላሽ የሚሰጠኝ አጥቻለሁ” በማለት አማራለች፡፡

አቶ ቴዎድሮስ ታደሰ የተባለው ግለሰብ በበኩሉ፤ ከጋምቤላ ክልል መዠንገር ዞን እንደመጣ ገልፆ፣ እህቱ ጨረቃ ታደሰ ወደ ሳውዲ አረቢያ ከሄደች ገና ሶስት ወር ቢሆናትም በሁለተኛው ወሯ ደውላ “ድረሱልኝ ከሞት አድኑኝ” የሚል ቃል ተናግራ ስልኩን መዝጋቷን ተናግሯል፡፡ “በራሴ ጥረት ደውዬ አገኘኋት፤ ወንድሜ ከሞት አድነኝ ሶስት ቦታ እያሰሩኝ በጣጥሰው ሊገድሉኝ ነው፡፡ ወደ ኤጀንሲ እሄዳለሁ ስል ጩቤ አውጥታ እቆራርጥሻለሁ ትለኛለች መሞቴ ነው” ብላ በጭንቀት ላይ ነን” በማለት ተናግሯል፡፡ አልጀዚር በተባለው ኤጀንሲ በኩል እንደሄደች የሚናገረው አቶ ቴዎድሮስ ኤጀንሲው ቦታ ይቀየርላታል ቢልም እስካሁን አለመየቀሯንና በስቃይ ውስጥ መሆኗን ኤጀንሲውም

ልጆቻቸውና ሚስቶቻቸው አረብ አገር የጠፉባቸው ቤተሰቦች ኤጀንሲዎችንና መንግስትን አማረሩ “ኤጀንሲዎችና ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ እልባት ሊሰጡን አልቻሉም”“የቤተሰቦቻችንን አድራሻ እና ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ተቸግረናል”

ሆነ የመንግስት መ/ቤት የሆነው ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጉዳዩን ችላ እንዳሉበት ተናግሯል፡፡

ከትግራይ ክክል አዲግራት የመጡት አቶ መሰለ መሀሪ የ70 አመት አዛውንት ሲሆኑ ልጃቸው ፊዮሪ ሲሆኑ ልጃቸው ፊዮሪ መሰለ ቦሌ ሩዋንዳ በሚገኘው ናይል ኤጀንሲ በኩል ሪያድ መሄዷን ጠቁመው በሄደች በ4 ወሯ ደውላ ከዚያ በኋላ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለች፣ ትኑር ትሙት የሚያውቁት እንደሌለ ጠቁመው ላለፉት 20 ወራት የልጃቸውን ሁኔታ ማወቅ እንዳልቻሉ በእንባ ገልፀዋል፡፡ “ለረጅም ጊዜ ወታደር ቤት ነበርኩኝ አካል ጉዳተኛም ነኝ ሰባት ልጆቼንና ባለቤቴን የማስተዳድረው በጡረታ ደሞዝ ነው” ያሉት አቶ መሰለ ልጃቸው ቤተሰቧን ለመርዳት ብላ ሄዳ ትሙት ትኑር አለማወቃቸውን ተናግረዋል፡፡ “ናይል ኤጀንሲ ለበርካታ ጊዜ ከትግራይ ስደውል የተለያየ ምክንያት ሲሰጡኝ ቆይተው በመጨረሻም ሪያድ ካለው ኤጀንሲ ጋር ያለን ግንኙነት ስለተቋረጠ ለመገናኘት ተቸግረናል የሚል ምላሽ ሰጥተውኛል” ሲሉ አማረዋል፡፡ ኤጀንሲው አክሎም ሪያድ ያለውን ኤጀንሲ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ክስ መስርተን እየተከራከርን ነው የሚል ምላሸ እንደሰጣቸውና በመጨረሻም ከትግራይ መጥተው ለሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ አቤት ብለው ምላሽ እስካሁን አለማግኘታቸውን ተናግረዋል።

አቶ ተሰማ ጉታ የተባለውና ከሰበታ ከተማ እንደመጣ የተናገረው ሌላው ባለ ጉዳይ ባለቤቱ ሞሚና አብደላ አራት ኪሎ በሚገኘው ተፈራ ኤጀንሲ በኩል ነሀሴ 2003 ዓ.ም ሳውዲ መሄዷንና በሄደች በዘጠኝ ወሯ እዛው በሚገኘው ቢሮ ደውላ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ከቤት አውጥተው ጥለውኛል በማለቷ ተጨንቆ እንደነበር ገልፆ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የሚስቱን ጉዳይ መስመር ለማስያዝ ወደ ተፈራ ኤጀንሲና ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሲመላለስ ቢቆይም መፍትሄ አለማግኘቱን ገልጿል፡፡ “አንድ ቀን ደውላ ሁለት የሌላ አገር ዜጐች አብረውኝ ይሰሩ ነበር ምን እንዳጠፉ ባላውቅም ታስረው የሶስት ሰው ስራ ተከምሮብኛል

የክልል መንግሥታት የወረዳ ባለሥልጣናት÷ የቤተ ክርስቲያን ሕንፃ እንዳይታነፅ፣ የመካነ መቃብር፣ የልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች እንዳይፈቀዱ፣ የቦታ ይዞታ ባለቤትነት በሕግ እንዳይረጋገጥ፣ ምእመናን ሥርዐተ አምልኮአቸውን በሰላምና በነጻነት እንዳይፈጽሙ፣ መብታቸውን ሲጠይቁም አፋጣኝና አግባብነት ያለው ፍትሕ እንዳያገኙ በማድረግ ተጽዕኖና በደል እያደረሱብኝ ነው ስትል የኦርቶዶክስ ቤ/ክርስትያን ወቀሰች፤ አቤቱታዋም በጥንቃቄ ታይቶ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣት አሳሰበች።

ቤተ ክርስቲያኒቱ ከጥቅምት 4 ቀን ጀምሮ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ ስታካሂድ በቆየችውና በዛሬው ዕለት እንደሚጠናቀቅ በሚጠበቀው ዓለም አቀፍ የመንበረ ፓትርያርክ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ፣ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ተወካዮች ‹‹የብዝኃነት አያያዝ፣ አክራሪነት/ጽንፈኝነት ዝንባሌዎቹና መፍትሔዎቹ›› በሚል ርእስ ጽሑፍ አቅርበዋል፡፡ ‹‹የሃይማኖት መቻቻል›› በሚለው የአጠቃላይ ጉባኤው መርሐ ግብር ላይ በቀረበው በዚህ ጽሑፍ÷ ሌሎች አገሮች ብዝኃነትን ይዞና አቻችሎ አንድነትን ለማስቀጠል ተግዳሮት እንደኾነባቸው፣ የብዝኃነት ተምሳሌትና መገለጫ በኾነችው ኢትዮጵያ ግን በየጊዜው ወደ አገሪቱ የገቡ ሃይማኖቶች፣ በሰላም የተቀባበሉበትና በመገናዘብ የኖሩበት ጥልቅ ትርጓሜና ታሪክ እንዳለው ተገልጧል፡፡

ጽሑፉን ተከትሎ በነበረው ውይይት በሰሜን ወሎ፣ በምዕራብ ወለጋ ሦስት ዞኖች፣ በጋሞጎፋ ሦስት ወረዳዎች፣ በሶማሌ ዘጠኝ ዞኖች፣ በደቡብ ጎንደርና በወላይታ ኮንታ በዴሳ ወረዳ የሌላ እምነት ተከታይ በኾኑ የመንግሥት ባለሥልጣናት በቤተክርስቲያኒቱ ላይ ይፈጸማሉ የተባሉ የመብት መደፈሮች፣ የአስተዳደር፣ የፍትሕና የጸጥታ አካላት አድልዎች በሀገረ ስብከቶቹ ሊቃነ ጳጳሳት በዝርዝር ተሰምተዋል፡፡

ዓለም አቀፍ ጉባኤው፤ ሲኖዶሱ የመንፈሳዊ ኮሌጁን ችግር እንዲፈታ አሳሰበ

የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ‹‹በወረዳ ባለሥልጣናት ተጽዕኖ እየተደረገብኝ ነው›› ስትል መንግሥትን ወቀሰች

ሊቃነ ጳጳሳቱ እንዳስረዱት÷ ለዞን መስተዳድር አካላት ውሳኔና መመሪያ የማይገዙ፣ የሌላ እምነት ተከታይ የኾኑና ሥልጣናቸውን ተጠቅመው ቤተ ክርስቲያኒቱን በፊውዳልነትና ነፍጠኛነት እየከሰሱ፣ ይዞታዋ እንዲነጠቅ ሕዝብን በበቀል ስሜት የሚያነሣሱ፣ በአማኞች ላይ አካላዊ ሥቃይና ሥነ ልቦናዊ ጫና በማድረስ ለመፈናቀልና ለሞት የሚዳርጉ፣ የሕዝቡን፣ የአገልጋዮችንና የሃይማኖት አባቶችን ጩኸት የማይሰሙ የወረዳ ባለሥልጣናት ጥቂቶች አይደሉም፡፡

በት/ቤት በአንገታቸው ማተብና መስቀል ያሠሩ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ተማሪዎች፣ ‹‹ከበላይ የመንግሥት አካል መምሪያ ተላልፎልናል፤ በሸሪዓ ሕግ ሴቶች ራሳቸውን እንዳይከናነቡ፣ ክርስቲያኖች ማተብና መስቀል እንዳያስሩ ተከልክሏል›› በሚሉ መምህራንና የፖሊስ አባላት ማተባቸው ከአንገታቸው ይበጠሳል፤ በጸሎተ ቅዳሴ ላይ ያሉ ምእመናን ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ በማስወጣት፣ ጸሎተ ቅዳሴው እንዲስተጓጎልና በበዓላት ቀን ሥራ እንዲሠሩም ይገደዳሉ፡፡ በሞትም በሕይወትም መደጋገፍ በሚታይባቸው ዕድሮችና በሕዝብ መጓጓዣዎች ሕዝቡ እንዳይረዳዳና እንዳይገለገል የወረዳ ዳኛ፣ ‹‹ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር አንድነት የለንም›› በማለት እስከ 80 ዓመት የቆየ ዕድር እንዲፈርስና ማኅበራዊ ግንኙነቶች እንዲታወኩ ምክንያት መሆኑ በስብሰባው ላይ በምሬት ተነግሯል፡፡

‹‹አንድ ሰው እግሩን እሳት እየበላው ቻል ይባላል? መቻቻል እስከ ምን ድረስ ነው?›› ሲሉ የጠየቁት የሰሜን ወሎ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ ‹‹እንድንቻቻል አድርጉን፤ እንችላለን›› ሲሉ የሚኒስቴሩን ተወካዮቹ አሳስበዋል፡፡

የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ተወካዮች በውይይቱ ላይ ክርስትና በአራተኛው መቶ ክ/ዘመን ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን የተናገሩ ሲሆን ሊቃነ ጳጳሳቱ መረጃው የተሳሳተ መሆኑን ጠቁመው ማስተካከያ ሰጥተዋል፡፡ ‹‹ከቤተ

ክርስቲያናችን አስተምህሮና ከመጽሐፍ ቅዱሱ ምስክርነት ጋር የሚጣረስ ነው፤ ክርስትናን የተቀበልነው ክርስቶስ ዐርጎ ዓመት ሳይሞላው፣ ሐዋርያትም ከኢየሩሳሌም ሳይወጡ በ34 ዓ.ም በጃንደረባው አማካይነት ከእግዚአብሔር ነው፤›› በማለት በቀጣይ የሚኒስቴሩ ተወካዮች በተመሳሳይ ርእሰ ጉዳይ በቤተ ክርስቲያኒቱ መድረኮች ተገኝተው ገለጻ ሲሰጡም፤ ክርስትና በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደገባ የሚጠቅሱትን አርመው እንዲቀርቡ መክረዋቸዋል፡፡

‹‹ክርስትና በአራተኛው መ/ክ/ዘ ወደ ኢትዮጵያ ስለመግባቱ የተናገሩት ዐፄ ኢዛና ክርስትናን በኦፊሴል ተቀብለው ያስፋፉበት ወቅት በመኾኑ ነው›› ሲሉ የተናገሩት የሚኒስቴሩ ከፍተኛ አማካሪ፤ በ34 ዓ.ም. ጃንደረባው እንደ ግለሰብ መቀበሉ ኢትዮጵያን ሊወክል ይችላል ተብሎ ከታመነ፣ ‹‹እኛ እናንተ ባላችሁት ለማስተካከል ችግር የለብንም፤ የተስማማችኹ ከኾነ በታሪክ መጻሕፍትም ሳይቀር እንዲስተካከል እናደርጋለን፤›› በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 27/2 ማንኛውም ሃይማኖት እምነቱን ለማስፋፋት ተቋማትን መመሥረት እንደሚችል፣ ለዚህም የቁጥር ገደብ እንዳልተቀመጠ ተወካዮቹ አውስተዋል፡፡

የተጠቀሱት በደሎችና ጥፋቶች በተጨበጠ ማስረጃ ተጠናክረው እንዲሰጧቸውና እነርሱን በተግባር በመፍታት በሂደት እንዲፈትኗቸው ያመለከቱት የሚኒስቴሩ ተወካዮች፣ ስሕተት በመንግሥትም በሃይማኖት አባቶችም ዘንድ እንዳለ፣ በታሪክ አጋጣሚ ወደ ኋላ በቀሩትና የመሠረተ ልማት ዝርጋታና ትስስር በሌላቸው ክልሎች ደግሞ ስሕተቱ እንደሚጎላ፣ ወቀሳውም እያንዳንዱ ቤተ እምነት በሁሉ ላይ የሚያሰማው እንደኾነ ጠቁመዋል፡፡

በሊቃነ ጳጳሳቱ ያልተነገሩ በየወረዳው ያሉ በርካታ

ቅሬታዎችን መከታተሉን የሚኒስቴሩ ተወካዮች ገልጸዋል፡፡ እንደ ጥፋት ደረጃውም ርምጃ የተወሰደበት ሁኔታና ተቀጥተው የተለቀቁ አካላት ስላሉ፣ በሕግ የተያዙት ጉዳዮች በሕግ እንዲያልቁ ሊቃነ ጳጳሳቱ ጠንክረው እንዲከታተሉ ጠይቀዋል፡፡

በሌላ በኩል ‹‹ኮሽ ባለ ቁጥር ወደ ቃሊቲ መፍትሔ ስለማይሆን›› ሚኒስቴሩ ግንዛቤ ላይ መሥራትን እንደሚያስቀድም፣ በሃይማኖት ተቋማቱም ዘንድ አስተምህሮውን ጠንቅቀው ያወቁ ሰባክያን ብቻ መሰማራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡ ‹‹እዚህ ተገኝታሁ ያቀረባችሁት ሐሳብ በጣም ጠቃሚ ነው›› በማለት ተወካዮቹን ያመሰገኑት ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ፣ ‹‹በየጊዜው መነጋገር ለሃይማኖትም ለጸጥታም የሚጠቅም ስለሆነ መማማሩ በአንድ ጊዜ የሚያበቃ ባይኾን ጥሩ ነው›› ሲሉ ውይይቱ እንዲቀጥል ያላቸውን ፍላጎት ገልጸዋል፡፡

በሌላ ዜና ዓለም አቀፍ ጉባኤው በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎችና በአስተዳደሩ መካከል በተማሪዎች አቀባበልና የምዝገባ ቀን፣ መምህራን ከኮሌጁ መኖርያ ቤቶች እንዲለቁ ከተላለፈው የአስተዳደሩ ትእዛዝና ከኮሌጁ ሌሎች የአሠራር ችግሮች ጋር ተያይዞ ሰሞኑን ዳግመኛ ላገረሸው ውዝግብ፤ በቅርቡ የሚካሄደው ቅ/ሲኖዶስ ኹነኛ መፍትሔ እንዲሰጠው መጠየቁ ተዘግቧል፡፡

ጥቃት ከገፅ 1 የዞረብሏል - ፖሊስ፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል፤ የፍንዳታው ፈፃሚዎች አልሸባብ መሆናቸውን ተጠይቀው ገና አልተረጋገጠም ብለዋል፡፡

የፀረ ሽብር ግብረ ሃይል ጉዳዩን እየመረመረ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ሽመልስ፣ ግብረ ሃይሉ የደረሰበት ውጤት ጊዜውን ጠብቆ ይፋ እንደሚደረግ አስረድተዋል፡፡

Page 4: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 4

ታኅሣሥ 29 ቀን 1992 ዓ.ም ተመሰረተዘወትር ቅዳሜ የሚታተም ሳምንታዊ ጋዜጣ

አሣታሚ አድማስ አድቨርታይዚንግ ኃ.የተ.የግ.ማ.

አታሚ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት

አራዳ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 17 / የቤት ቁ.984

አድራሻ:- ካዛንችስ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚ/ር ገባ ብሎ ከጤና ጣቢያው ጀርባ ቂርቆስ ክ/ከ ቀበሌ 31 የቤት ቁ.376

ስልክ 0115-155-222/ 0115-153-660 ሞባይል 0921-622-040/0911-201-357 ፋክስ 0115-547373 ፖ.ሳ.ቁ 12324

E-mail :- [email protected]/[email protected]/ website www.addisadmassnews.com

ሥራ አስኪያጅ:- ገነት ጎሳዬ (ልደታ ክ/ከ ቀበሌ 04/06 የቤ.ቁ.581) ስልክ 0911-936787

ዋና አዘጋጅ:- ነቢይ መኮንን (ቂ/ክ/ከ ቀበሌ 08/09 የቤት.ቁ.213)ም/ዋና አዘጋጅ:- ኢዮብ ካሣ

ከፍተኛ አዘጋጅ:- ሰለሞን ገ/እግዚአብሔር አዘጋጅ:- ኤልሳቤት ዕቁባይ

ከፍተኛ ሪፖርተሮች:- መንግስቱ አበበ፣ ግሩም ሠይፉ፣ አበባየሁ ገበያው፣ መልካሙ ተክሌ፣ መታሰቢያ ካሳዬ፣ ሰላም ገረመው፣ ናፍቆት ዩሴፍ፣ አለማየሁ አንበሴሌይ አውት ዲዛይነር:- ኮክ አሰፋ፣ ንግሥት ብርሃነ አርቲስት:- ሠርፀድንግል ጣሰው፣ ሽያጭና ስርጭት:- ሰለሞን ካሣ፣ ፎቶግራፈር:- አንተነህ አክሊሉ ዌብፔጅ:- አሰቴር ጎሳዬ፣ ኮምፒውተር ጽሑፍ:- የወብዳር ካሣ

`°e ›”kî ገቢዎች ከገፅ 1 የዞረተከሳሾችም በክሱ ላይ ያላቸውን የመቃወሚያ

ነጥብ ያስመዘገቡ ሲሆን አቶ ዮሴፍ አዳዩ የተከሰሱበት የወንጀል አንቀጽ ከ10 አመት በታች የሚያስቀጣ በመሆኑ የዋስትና መብታቸው ተከብሮላቸዋል፡፡

አቃቤ ህግ በአቶ ማሞ ኪሮስ ላይ ያቀረበው ክስ ተከሳሹ በ1998 ዓ.ም “ከተማ ኮንስትራክሽን ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ”ን በስራ አስኪያጅነት ሲመሩ ከህግ አግባብ ውጪ እቃዎች ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ አድርገዋል ይላል፡፡ ተከሳሹ “የኮንክሪት ሚክሰር” እና “ቫይብሬተር” ከውጭ ከቀረጥ ነፃ ካስገቡ በኋላ፣ ከእሸቱ ኤልያስ ወልደማርያም አስመጪና ላኪ የገዙ ለማስመሰል ሃሰተኛ ሰነድ አዘጋጅተዋል የሚል የወንጀል ክስም ቀርቦባቸዋል፡፡ አቃቤ ህግ በክስ መዘርዝሩ ላይ ስለወንጀሉ አፈፃፀም ያስረዱልኛል ያላቸውን የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎች ማቅረቡንም ፍ/ቤቱ የክሱን ጭብጥ በንባብ ባሰማበት ወቅት አመልክቷል፡፡ ክሱ በችሎቱ ከተነበበ በኋላም የቀረበው ክስ የውስብስብነት ባህሪ ስለሌለው በመደበኛ ክርክር ሂደት እንዲቀጥል ብይን ተሰጥቷል፡፡

የተከሳሽ ጠበቃ የመቃወሚያ ሃሳባቸውን ተጠይቀው ሲያቀርቡም፤ የአቃቤ ህግ ክስ፣ ተከሳሽ ራሱን መከላከል በሚያስችለው ደረጃ ተዘርዝሮ በሚገባ የቀረበ አይደለም፣ የተጠቀሰው የወንጀል አንቀጽ (379) በባህሪው የሙስና ወንጀልን አያመለክትም፤ ክሱ የቀረበበት አንቀጽ ተገቢ አይደለም” ብለዋል፡፡ ከእሸቱ ኤልያስ ድርጅት ተጭበረበረ የተባለው ሰነድ የመንግስት ሰነድ አይደለም ያሉት የተከሳሽ ጠበቃ፤ ክሱ በዚህ መልኩ መቅረቡ የተከሳሹን የመከላከል እድል የሚያጠብ ስለሆነ ተሻሽሎ እንዲቀርብ ይደረግልን ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ አቃቤ ህግ በበኩሉ፤ ለመቃወሚያው በሰጠው ምላሽ ክሱ ተከሳሹ በሚረዳው መልኩ በዝርዝር የቀረበ ነው፣ የተጠቀሰው አንቀጽ የሙስና ወንጀልን የሚጠቅስ ነው፣ የተጭበረበረው ሰነድ በእርግጥም ከግል ድርጅት የወጣ ነው፤ ነገር ግን የጉምሩክ መስሪያ ቤትን በዚያ ሰነድ አሳስተዋል፤ ስለዚህ ፍ/ቤቱ መቃወሚያውን ውድቅ ያድርግልን ሲል ጠይቋል፡፡

በተመሳሳይ ፍ/ቤቱ በአቶ ዮሴፍ አዳዩ ላይ የቀረቡትን ሁለት ክሶች በንባብ ያሰማ ሲሆን አንደኛው ክስ፣ ተከሳሽ በገቢዎችና ጉምሩክ የአዲስ አበባ ኤርፖርት የመንገደኞች ማስተናገጃ የፍተሻ ክፍል ሃላፊ ሆኖ በሰራባቸው ከ2002 -2003 ባሉ አመታት ከውጭ ወደ ሃገር ውስጥ የሚገቡ የተለያዩ ግለሰቦች ለያዙት እቃ ቀረጥ ሳይከፍሉ እንዲገቡ በማሰብ፣ ሳይፈተሹ እንዲያልፉ አድርጓል የሚል ነው፡፡ ከዚሁ ክስ ጋር ተያይዞም ንብረትነታቸው የገቢዎችና ጉምሩክ የሆኑ ኦርጅናል የስራ ሰነዶችን መኖሪያ ቤቱ አስቀምጦ ተገኝቷል የሚል የወንጀል ክስ ቀርቦበታል፡፡ በተከሳሹ ላይ የቀረበው ሁለተኛ ክስ ደግሞ ህጋዊ ፍቃድ የሌለው ማካሮቭ ሽጉጥ ይዞ ተገኝቷል የሚል ነው፡፡ ለክሶቹ የሰነድና የሰው

ማስረጃ እንዲሁም በኤግዚቢት የተያዙ ንብረቶች መቅረባቸውን በክሱ ማመልከቻ ተጠቅሷል፡፡

የተከሳሽ ጠበቃ የመቃወሚያ ሃሳባቸውን ያቀረቡ ሲሆን ወንጀሉ ተፈፀመ የተባለበት ትክክለኛ ቀን በዝርዝር አልተገለፀም፣ የግለሰቦቹ ማንነትና ብዛት በግልጽ መታወቅ ነበረበት፣ የጉምሩክ ሰነዶች በቤቱ ተገኝተዋል የተባለው በየትኛው የወንጀል አንቀጽ እንደሚያስጠይቅ አልተጠቆመም ብለዋል፡፡ ፍቃድ የሌለው መሣሪያ ይዞ መገኘት የሚለውን በተመለከተም ኮሚሽኑ እንዲህ አይነት ክስ ማቅረብ አይችልም፤ ጉዳዩ ከሙስና ጋር የሚገናኝ ስላልሆነ በሌላ አካል ነው መታየት ያለበት ስለዚህ ክሱን ይሰርዝ ሲሉ ጠበቃው መቃወሚያቸውን አቅርበዋል፡፡

አቃቤ ህግ ለመቃወሚያው በሰጠው ምላሽ፤ ድርጊቱ የተፈፀመው በተለያየ ጊዜ ነው፣ ሳይፈተሹ እንዲያልፉ የተደረጉት ግለሰቦች ብዛት እና ማንነት ምስክሮች ሲቀርቡና ማስረጃ በዝርዝር ሲቀርብ በሂደት የሚታይ ይሆናል፣ ሰነዶችን በተመለከተም ኦርጅናል የመስሪያቤቱን ሰነዶች ማስቀመጥ የነበረበት መኖሪያ ቤቱ ሳይሆን መስሪያ ቤት ነው ብሏል፡፡ ህገ ወጥ መሣሪያ ይዞ መገኘት በእርግጥ የሙስና ወንጀል አይደለም፤ ነገር ግን ክሱን አብሮ ለማቅረብ የስነ ስርአት ህጉ እንደሚፈቅድ በሰበር ሰሚ ችሎት ተወስኗል የሚል ምላሽ ሰጥቷል - አቃቤ ህግ፡፡

የተከሳሹ አቶ ዮሴፍ አዳዩ ጠበቃም የተጠቀሰው አንቀጽ ከ10 አመት በታች የሚያስቀጣ ስለሆነ የዋስ መብትን የሚያስከለክል አይደለም፤ የዋስትና መብቱ ይከበር ሲሉ ፍ/ቤቱን የጠየቁ ሲሆን አቃቤ ህግም በዋስ ቢለቀቁ ተቃውሞ እንደሌለው፣ ነገር ግን ከሃገር እንዳይወጡ ለኢምግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ትዕዛዝ ይፃፍልን ሲል አመልክቷል፡፡

የግራ ቀኙን ክርክር ሲያደምጥ የቆየው ፍ/ቤቱ፤ በአቶ ዮሴፍ አዳዩ ላይ በሰጠው ትዕዛዝ፣ ተከሳሹ የ5ሺህ ብር ዋስ አቅርበው እንዲለቀቁ እንዲሁም ከሀገር እንዳይወጡ ለኢምግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ደብዳቤ እንዲፃፍ ብሏል፡፡ መዝገቡንም ለጥቅምት 25 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡ በአቶ ማሞ ኪሮስ ላይ ፍ/ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ፣ መቃወሚያውን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 14 ቀን 2006 ቀጥሯል፡፡

በሌላ በኩል ክስ ሳይመሰረትባቸው ጉዳያቸው ወደ ምርመራ መዝገብ የተመለሠው አቶ ፍፁም ገ/መድህን፣ በእግዚአብሔር አለበልና ምህረተአብ አብርሃ ጥቅምት 6 ቀን 2006 ፍ/ቤት ቀርበው ዳኞች ተሟልተው ባለመቅረባቸው ለጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡

አቶ መላኩ ፋንታ እና አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ጨምሮ ክስ ቀርቦባቸው ማረሚያ ቤት የሚገኙ ባለስልጣናትና ባለሀብቶች ጥቅምት 11 እና 12 ቀን 2006 ዓ.ም ክሣቸውን ለማንበብ ቀጠሮ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

ተመራቂዎች ከገፅ 2 የዞረ

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ የሥነ - ከዋክብት ተመራማሪ በአንድ የገጠር ከተማ ይኖር ነበረ፡፡ የዚህ ሰው የሁልጊዜ ፈሊጥ ማታ ማታ ከቤቱ እየወጣ የሰማይ ላይ ከዋክብትን ማየትና የሰው ልጆችን ዕጣ -ፈንታና የተፈጥሮን አካሄድ መመርመር ነበር፡፡

ይህን ክህሎቱን ከጊዜ በኋላ የተረዱ የከተማይቱ ሰዎች ቀስ በቀስ ስለሱ አዋቂነት ማውራት ጀመሩ፡፡ ዋሉ አደሩና እየተከተሉት ዕጣ - ፈንታቸውን ይጠይቁት ያዙ፡፡

አንደኛው - “የሥነ - ከዋክብት አዋቂ ሆይ! የእኔ የወደፊት ዕጣ ምን ይሆን?” ሲል ጠየቀው፡፡ አዋቂ - “ያንተን የከዋክብት ፈለግ እንዳየሁት የመጨረሻ ዕልፈትህ ጠብ ውስጥ ገብተህ ነው፡፡

ያላሰብከው ሰው ነው የሚገድልህ” አለው፡፡ አንደኛው - “ታዲያ ምን ባደርግ ነው የሚሻለኝ?”አዋቂ - “በምንም ዓይነት ጠብ አካባቢ አትገኝ” ሌላ ተከታዩ ይመጣል፡፡ “አዋቂ ሆይ! የእኔስ ዕጣ ምን ይሆን?”አዋቂ - “ኮከብህ የብልጽግና ነው፡፡ ነገር ግን ምቀኞች አሉብህ” ተከታይ - “ታዲያ ምን ባደርግ ከእነዚህ ምቀኞች ተንኮል አመልጣለሁ?”አዋቂ - “ደግ እየመሰሉ ከሚቀርቡህ ሰዎች ተጠንቀቅ” እንዲህ እንዲህ እያለ በየጊዜው እየተከተሉ ዕጣ - ፈንታቸውን ለሚጠይቁት ሰዎች መልስ ሲሰጥና

ሲመክር ሰነበተ፡፡ አንድ ማታ እንደተለመደው ከከተማው ዋና በር (ከተምበሪ) አልፎ ሄደ፡፡ ቀና ብሎ ዐይኖቹን ሰማዩ ላይ ተከላቸው፡፡ መመራመሩን፣ መጠበቡን፣ መፈላሰፉን ቀጠለ፡፡ ይህን

የየከዋክብቱን አካሄድና እንቅስቃሴ እያየ፣ እንዳንጋጠጠ፣ መራመዱን ቀጠለ፡፡ ሳያስበው ከእግሩ ሥር ካለ አንድ ደረቅ ጉድጓድ ውስጥ ድንገት ጥልቅ አለ፡፡

እዚያ ጉድጓድ ውስጥ ሆኖ እንደወቀደ ያጓራና ያቃስት ገባ፡፡ አንድ ሰው በዚያ አቅራቢያ ሲያልፍ የዚያን የሚያስጓጉር አዋቂ ድምጽ ሰማ፡፡ ወደ ጉድጓዱ አፍ ቀረበና ቁልቁል ተመለከተ፡፡ ሁኔታውን ካስተዋለ በኋላ፤

“ምን ልታደርግ እዚያ ገባህ?”“ወድቄ ነው”“እንዴት ይሄን የሚያህል ጉድጓድ አላየህም?” “ሰማዩ ላይ በጣም አተኩሬ ስለበረ ነው”“አይ ወዳጄ!” እንደዛ ታላቅ አዋቂ ነህ ብለን የተቀበልንህ ሰው፤ ሰማይ ሰማይ ስታይ እግሮችህ ወዴት

እንሚወስዱህ እንኳ ካላወቅህ፤ እኔ እንደሚሰማኝ፤ አሁን ያለህበት ቦተ ተገቢ ቦታህ ነው!” አለው፡፡ * * *

ሰማይ ሰማይ ስናይ እግራችን ሥር ያለውን ነገር አንዘንጋ፡፡ ሰማዩን አተኩረን ስናይ ቀልባችን ሙሉ በሙሉ እሱ ላይ ብቻ ካረፈ፤ ከሥር እግራችንን የሚመታንን እንቅፋትና የሚያሰምጠንን ጉድጓድ አናየውም፡፡ ወደኃያላን መንግሥታት ስናንጋጥጥ የራሳችንን ህዝብ እንረሳለን፡፡ አልፈን ተርፈንም የሰዎችን ዕጣ-ፈንታ ስንናገር የራሳችንን ዕጣ-ፈንታ ሳናቅ እንዳንቀር እንጠንቀቅ!

ኃያላን መንግሥታት ሲሻቸው የበኩር ልጅ፣ ሲሻቸው የእንጀራ ልጅ ማድረግን ይችሉበታል፡፡ ኃያላን መንግሥታት “ሲሞቅ በማንኪያ ሲቀዘቅዝ በእጅ” ገንፎ መብላትን ያውቁበታል፡፡ መልዕክተኞቻቸውን ሲሻቸው በእርዳታ ሰጪ መልክ፣ ሲሻቸው በሚሲዮናውያንና በሃይማኖተኞች መልክ፣ ሲሻቸው በዲፕሎማት መልክ፤ ካልሆነም በቀጥታ ስለላ መልክተኞች - አሊያም በቱሪስት ወይም በፒስኮር መልክ ይልካሉ፡፡ ከከፋም የውስጥ ዐርበኛ ይቀጥራሉ፡፡ ላላ ያለ ካገኙም አገራቸው ድረስ ጋብዘው፣ አስተናግደው ሾመው፣ ሸልመው አንቱ ብለው ይቀባሉ፡፡

ያለ፣ የነበረ ወደፊትም የሚኖር ዘዴያቸው ነው፡፡ ይሄ ሁሉ ካልተሳካ የቁርጡ ቀን መጣ ማለት ነውና እንደ ኢራቅ የጦር ዘመቻ ያካሂዳሉ፡፡ እንደግሎባላይዜሽን አበጋዞች ሳይሆን እንደጥንቶቹ ቅኝ ገዢዎች- በግልጽ ወረራ ያካሂዳሉ፡፡

ከሁሉም ይሰውረን፡፡ ሲያወድሱ ሰማይ፣ ሲጥሉ እንጦር አውርደው ከትቢያ ይደባልቃሉ፡፡ የሁልጊዜ መሳሪያቸው ነው፡፡ እስካመቸናቸው እስካልቆረቆርናቸው ድረስ ያለእኛ በትክክለኛው የዕድገት መስመር ላይ ያለ አገር አይገኝም፡፡ “እንዲህ እያልሽ ውቴልሺን ሽጪ” እንዳለው ወሎ፤ የሚነግራቸው ጠፍቶ ነው፡፡ ለእነሱ የከፋን ለታ ግን ያለእኛ ኋላቀር፣ ያለእኛ ደንቆሮ፣ ያለእኛ ጦርነት ናፋቂ፣ ያለእኛ ረሃብተኛ፣ ያለእኛ መናጢ ደሃ የለም፡፡ ”እፀድቅ ብዬ ባዝላት ተንጠልጥላ ቀረች” ይሉናል፡፡

ከበረታን፤ “አላህንም አትክዳ፣ ሐረጓንም አትልቀቅ” እንዳሉት ጠቢብ ማሰብ አለብን፡፡ የኃያላኑን የቢዝነስ ኮሙኒቲ አይተን እኛ ምን እንሥራ ማለታችን ደግ ነገር ሆኖ፤ ከእዚህ ሁሉ

በስተጀርባ ምን አለ? ብሎ መጠየቅ ያባት ነው፡፡ ምን ያህል ከልባቸው ነው? እነሱ፤ ለህዝባችን ይበጃል ያሉትን ማንኛውንም እኩይ ተግባር ከመፀፈም ወደኋላ ብለው ያውቃሉን? ብለን እንጠይቅ፡፡ ሁሉንም በትጋት በጉጉት - ዐይን እናስተውል፡፡

የፖለቲካ ፀሐፍት እንደሚነግሩን፤ “ሥልጣን ላይ ያሉ ሰዎች የሚወድቁት ስህተት ስለሚሰሩ ሳይሆን ስህተታቸውን እንዴት እንደሚያርሙ ስለማያውቁ ነው፡፡ ይሄ የእኛም ችግር ነው፡፡ ሁለት ተጠቃሽ ባህሪዎቻችን፡- “ካፈርኩ አይመልሰኝ (Rigidity)”፣ እና “የአብዬን እከክ ወደእምዬ ልክክ (Blame shifting)” ናቸው፡፡ የሠራሁት ነገር ስህተት እንዳለበት ቢነገረኝም አልለቀውም፡፡ አንዴ አድርጌያለሁ ብያለሁ፡፡ ብያለሁ፡፡ ኃያላኑም ተናግረዋል፤ ማለት አይበጅም፡፡ በተቻለ መጠን በኃያላን ውዳሴ አለመማለል ብልህነት ነው! “ቅጥ - ያጣ መረጃ” ይዘን ነው እስካሁን የሄድነው ተብሏል፡፡ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ችግሮቻችን፣ የሚጨበጡትንና የማይጨበጡትን ጨምሮ፤ ስፍር - ቁጥር የላቸውም፡፡ በአንድ የድህነት ባኮ ከትተን ልንገላገላቸው መንገድ ከጀመርን ከራርመናል፡፡ አሁንም ግን በመጨለምና በንጨላጨል መካከል ነን፡፡

በሬዲዮ ጥያቄና መልስ ፕሮግራም “የሱዳን ዋና ከተማ ማን ትባላለች” ሲባል “አማርኛ ይሁንልኝ” …“የቆጡን አወርድ ብላ…” ጨርሰው ሲባል “ስፖርት ይሁንልኝ”፤ ዓይነት መልስ የሚመልስ ህብረተሰብ ይዘን እየዳከርን ነው፡፡ አገራችን፤ ላዩም ታቹም ይሄን መሳይ ነው!

በጭካኔ ፍትሕን ማምጣት (Brutal justice) እና የኢኮኖሚ አምባገነንነት (Economic Dictatorship) ቦታ ቦታ አላቸው፡፡ ጊዜ ጊዜም አላቸው፡፡ ለመተግበር ፍፁም ጥንቃቄን ይጠይቃሉ። ውጤታቸው ጠላት ማብዛት፣ ዜጋን ማስኮረፍ፣ ሕዝብን መሬት ውስጥ መክተት ሊሆን ይችላል፡፡ ሆደ - ሠፊና ለጋሥ አምባገነን መሆን (Benevolent Dictator) የዋዛ ነገር አይደለም፡፡ ህብረተሰብን በቅጡ ማሳመን ይሻል፡፡ በተለይም የተለያየ ሃይማኖት፣ ባህልና ብሔረሰብ ባለበት አገር እጅግ ከባድ አስተዳደራዊ ምሉዕነትን ይጠይቃል፡፡ የፈረንሳዩ መሪ ደጐል “ሶስት መቶ ስልሳ ዓይነት ዐይብ ያለውን ህዝብ ማስተዳደር ከባድ ነው” የሚለን ለዚህ ነው!

“ሶስት መቶ ስልሣ ዓይነት ዐይብ ያለውን ህዝብ ማስተዳደር ከባድ ነው”

የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ደጐል

ምስጋናውን ስለ ጉዳዩ ጠየቀናቸው በሰጡት ምላሽ፤ ችግሩ መኖሩን አምነው፤ ከፌደራል እስከ ክልል ካሉ የሲቪል ሠርቪስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ጋር ግንኙነት በመፍጠር ችግሩን ለመፍታትና ተመራቂዎች በተማሩበት መስክ የስራ እድል እንዲያገኙ ጥረት

መደረጉንና አሁንም ጥረቱ እንደቀጠለ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ “ችግሩ ጐልቶ የሚታየው አዲስ አበባ ባሉ የ2003 ተመራቂዎች ላይ ሲሆን በተቀሩት አመታት የተመረቁ በርካታ ተማሪዎች የትምህት ክፍሉ ባደረገው ጥረት በአማራ፣ በትግራይና

ተመራቂዎች ወደ ገፅ 26 ዞሯል

Page 5: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 5 ’í ›e}Á¾ƒ

ምርመራ ወደ ገፅ 24 ዞሯል

ዜጐች ወደ ገፅ 26 ዞሯል

በአድዋ ጦርነት የተጎዱ ወታደሮች እንዲታከሙና እንዲያገግሙ በማሰብ ነው አፄ ምኒልክ በአገሪቱ የመጀመሪያውን ሆስፒታል የመሰረቱት፡፡ ዛሬ

ዳግማዊ ምኒልክ ሪፈራል ሆስፒታል የቀዶ ጥገና፣ የውስጥ ደዌ እና የአጥንት ህክምና አገልግሎቶችን የሚሰጥ ቢሆንም ግማሽ ያህሉ ህመምተኞች ለአይን ህክምና የሚመጡ ናቸው፡፡ ባለፈው አመት ተኝተው የሚታከሙትንና ቀዶ ህክምና የሚያስፈልጋቸውን 82ሺህ ተመላላሽ ታካሚዎችን አስተናግዷል፡፡

ዋነኛ የህክምና አገልግሎቶችን ወደ አራት ለማሳደግ ህንፃ እያስገነባ መሆኑን የገለፁት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ሞገስ መስፍን፤ ግንባታው ሲጠናቀቅ የእናቶችና ህፃናት ህክምናን እንደሚጀምር ገልፀዋል፡፡

ብዙውን ጊዜ የምኒልክ ሆስፒታል ስም የሚነሳው ግን በአስከሬን ምርመራ አገልግሎት ነው፡፡ በ1965 ዓ.ም የተቋቋመው የአገሪቱ ብቸኛ የአስክሬን ምርመራ ክፍል፣ በቀን በአማካይ ሰላሳ አስከሬኖችን ይመረምራል፡፡ በመጀመሪያዎቹ 15 ዓመታት የአስክሬን ምርመራው ላይ ሦስት ኢትዮጵያውያን የህክምና ባለሙያዎች መስራታቸው

ለ15 ዓመታት ምርመራውን የሚያካሂዱት የኩባ ሃኪሞች ብቻ ናቸውሦስት ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ራሳቸውን አጥፍተዋል

ከ31 ዓመት በላይ የሆነው የአስክሬን ምርመራ ክፍል

ሰላም ገረመው የሚታወስ ቢሆንም፣ ሶስቱም እራሳቸውን

አጥፍተው መሞታቸውን በተመለከተ ስራ አስኪያጁ ማረጋገጫ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ ከዚያ ወዲህ በአስከሬን ምርመራ ክፍል ውስጥ የሚሰራ ኢትዮጵያዊ ባለሙያ አለመገኘቱ ግን እውነት ነው። ሆስፒታሉ የኩባ ሃኪሞችን ስድስት ዓመት የስራ ውል እያስፈረመ ማስመጣት የጀመረውም በዚህ ምክንያት ነው፡፡ አሁን እየሰሩ ያሉት የአስክሬን ምርመራ ብቸኛ ኩባዊት ባለሙያ ግን የሁለት አመት ውል ነው የፈረሙት፡፡ ኩባዊቷ ሃኪም በአዲሱ አመት መግቢያ ላይ የጤና እክል ሲገጥማቸው የአስክሬን ምርመራ ለሦስት ቀናት ከመስተጓጎሉም በተጨማሪ፣ ባለፈው ሳምንት የስራ ውላቸውን በማጠናቀቃቸው፣ የአስክሬን ምርመራ ክፍል ተዘግቶ ነበር፡፡ የሆስፒታሉ ምንጮች እንደሚሉት፤ ኩባዊቷ ሃኪም በ6000 ብር የወር ደሞዝ ነው ሲሰሩ የቆዩት። ከ400 ዶላር በታች መሆኑ ነው፡፡ አሁን ሌሎች ሃኪሞች ከኩባ እስኪመጡ ድረስ ሃኪሟ በ800 ዶላር ክፍያ ለአንድ ወር በስራቸው ላይ እንዲቆዩ ተደርጓል፡፡

መንግስት የአስክሬን ምርመራ ክፍሉን ያቋቋመው፣ በደል የደረሰባቸው ዜጎች ፍትህ እንዲያገኙ በማሰብ ነው የሚሉት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ሞገስ፤ ወንጀል የተፈፀመበትንና ያልተፈፀመበትን በሳይንሳዊ ምርመራ እየለየን የፍትህ አካላትን እናግዛለን ብለዋል፡፡ እንዲያም ሆኖ የአስክሬን ምርመራ ክፍል በየጊዜው በርካታ ትችቶች

እንደሚሰነዘሩበት ይታወቃል፡፡ በአስተዳደር ችግሮችና በአሰራር ጉድለቶች የተነሳ እንግልት እንደሚደርስባቸው ተገልጋዮቹ ይናገራሉ፡፡ የሟች ቤተሰቦች አስከሬን ለመውሰድ ሲመጡ፣ የሌላ ሰው አስከሬን ተቀይሮ ይሰጣቸዋል የሚል ቅሬታም በተደጋጋሚ ይሰማል፡፡ ኩላሊት ይሰርቃሉ የሚል ውንጀላም አልፎ አልፎ ይሰነዘራል፡፡

ኩላሊት ተሰርቆ ይወሰዳል የሚለው ውንጀላ፣ መሰረት የሌለው አሉባልታ ነው የሚሉት አቶ ሞገስ፤ “ፈፅሞ አይደረግም፤ ሊደረግም አይችልም” ብለዋል።

በእርግጥ፣ የኩላሊት ስርቆት ከፍተኛ ወንጀል ስለሆነ፣ እንኳን ኢትዮጵያ ውስጥ ቀርቶ ሌሎች አገራት ውስጥም በቀላሉ የሚፈፀም ወንጀል አይደለም፡፡ ነገር ግን ህገ ወጥ በመሆኑ ብቻ አይደለም ኩላሊት የማይሰረቀው፤ የሰውነት አካል ወስዶ ወደ ሌላ ሰው ለማስተላለፍ የዘመኑ ቴክኖሎጂ ያፈራቸው የረቀቁ መሳሪያዎች እንደሚያስፈልጉት አቶ ሞገስ ገልፀው፣ ለኩላሊት ስርቆት የሚሆን ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ብለው እንደማያምኑ ይናገራሉ። ከአስክሬን ምርመራ ጋር ተያይዞ የኩላሊት ስርቆት በጭራሽ ሊፈፀም እንደማይችል በቀላሉ መገንዘብ ይቻላል የሚሉት አቶ ሞገስ፤ አንድ ሰው ከሞተ በኋላ ለህክምና የሚያገለግል የአካል ክፍል ይኖረዋል ወይ ብለን መጠየቅ አለብን ብለዋል፡፡ አቶ ሞገስ እንደሚሉት፤ ከአስክሬን ተሰርቆ የሚወሰድ ኩላሊት ሊኖር አይችልም፡፡ ለነገሩ፣ ከአረብ አገራት

በተለያዩ ምክንያቶች ሞተው የሚመጡ አስከሬኖች ላይም አንዳችም የአካል ክፍል ስርቆት አጋጥሞ እንደማያውቅ ባለሙያዎች ይመሰክራሉ፡፡ እንዲያም ሆኖ አከራካሪ ነገሮች መፈጠራቸው አልቀረም። ለምሳሌ የአይን ብሌን ከሟቾች አካል መውሰድ እንደሚቻል እና እንደሚወሰድ ይታወቃል፡፡ በአንድ በኩል በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የአካል ክፍል “ልገሳ” መልካም ነው፡፡ ያለ ፈቃደኝነት የሚከናወን የአይን ብሌን “ልገሳ” ሲኖር ግን ያሳስባል። የሆነ ሆኖ፣ አስከሬን ወደ ሆስፒታሉ የሚመጣው በፖሊስ ፍቃድ ብቻ እንደሆነና ያለ ፖሊስ ፍቃድ ሆስፒታሉም አስከሬን እንደማይቀበል አቶ ሞገስ ይገልፃሉ፡፡ መንገድ ላይ ሞቶ ሲገኝ፣ በሰው እጅ ተገድሏል ተብሎ ሲጠረጠር፣ ቤተሰብ በጥርጣሬ እንዲመረመርለት ሲጠይቅ፣ በማረሚያ ቤት ህይወቱ ካለፈ፣ ከአረብ አገር አስክሬን ሲመጣ ምርመራ ይካሄዳል፡፡ የሆስፒታሉ የአስክሬን ምርመራ ለፖሊስ ትልቅ ዋጋ አለው፡፡ የወንጀል ድርጊት መፈፀሙንና አለመፈፀሙን ለማወቅ ብቻ ሳይሆን፣ የወንጀል አፈፃፀሙንና የወንጀለኛውን ማንነት ለማወቅ ይጠቅማል፤ የአስከሬን ምርመራ፡፡

የአስከሬን ምርመራ ወንጀለኞችን ለመያዝ የመጥቀሙን ያህል፣ የተሳሳቱ ጥርጣሬዎችን ለመከላከል እንደሚረዳ አቶ ሞገስ ሲገልፁ፤ አንድ ገጠመኝን ይጠቅሳሉ፡፡ የመኪና አደጋ የደረሰበት አንድ ወጣት በህክምና ድኖ ስራውን ይጀምራል። ጉዳት ያደረሰውም አሽከርካሪ፣ ከተጎጂ ቤተሰብ ጋር በመስማማቱ ክስ አልተመሰረተበትም፡፡ ተጎጂው ወጣት ታክሟል፡፡ ከአንድ አመት በኋላ ግን ህይወቱ አለፈ፡፡ የሟቹ ቤተሰብም ለፖሊስ አመለከቱ፤ ልጃችን የሞተው ከአመት በፊት በደረሰበት ግጭት ነው አሉ፡

“ትልልቅ ፕሮጀክቶች በውጭ ምንዛሬ እጥረት እየተቀየዱ የሚሄዱበት እድል ሰፊ ነው” … የኤክስፖርት ገቢ መዳከሙን በመግለፅ ይህን የተናገሩት የንግድ ሚኒስቴር ሃላፊዎች ናቸው። ያሳስባል፣ እውነታቸውን ነው። ነገር ግን፣ ትልቁና አሳሳቢው ነገር፣ የመንግስት ፕሮጀክቶች መስተጓጎላቸው አይደለም። የውጭ ንግድ መዳከም፣ ጠቅላላ በአገር ኢኮኖሚና በዜጎች ኑሮ ላይ ተጨማሪ ችግር እንደተደቀነ የሚጠቁም ምልክት ነው። ደግሞስ፣ የመንግስት ገናናነት እየገዘፈ፣ የግል ኢንቨስትመንት እየቀጨጨ፣ እንዴት ጥሩ ውጤት ይገኛል ብሎ መጠበቅ ይቻላል?

አሳዛኙ ነገር፣ መንግስት ራሱን በራሱ ጠልፎ እየጣለ መሆኑን አለመገንዘቡ ነው። መንግስት “የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ” ውስጥ የዘረዘራቸውን ትልልቅ ፕሮጀክቶች ለማሳካት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ያስፈልገዋል። ግን ምን ዋጋ አለው? ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ የሆነው የግል ኢንቨስትመንት እየቀጨጨ የመጣው፣ “በእድገትና ትራንፎርሜሽን እቅድ” ሳቢያ ነው። ተግባራዊ የተደረጉ የመንግስት እቅዶች፣ የኤክስፖርት ገበያውንና የውጭ ምንዛሬ ምንጮችን እንዴት እየጎዱ እንደሆነ ለማሳየት እሞክራለሁ።

በእርግጥ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ በውጭ ምንዛሬ እጥረት ሳቢያ የሚስተጓጎል ፕሮጀክት የለም ብለዋል። የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በጭራሽ አይጓተትም ያሉት ጠ/ሚ ኃይለማሪያም፣

የውጭ ንግድ ፈቅ አላለም፤ ባለበት ደንዝዞ ቆሟል - የንግድ ሚኒስቴር መረጃ።የግል ኢንቨስትመንት ተዳክሟል፤ ድርሻው በግማሽ ቀንሷል - የIMF መረጃ።የአገሪቱ የባንክ ብድር፣ 90% ወደ መንግስት ይሄዳል - የአለም ባንክ ሪፖርት።

ዜጎችን እያቀጨጨ የሚፈረጥም መንግስት… ብዙ አይራመድም ስንት እድሜ ይኖረዋል?

ሌሎቹ ትልልቅ ፕሮጀክቶች ደግሞ በውጭ ብድር የሚካሄዱ በመሆናቸው የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደማያሳስብ ለመግለፅ ሞክረዋል።

እንዲያም ሆኖ፣ ከኤክስፖርት የሚገኘው ገቢ የታሰበውን ያህል እንዳልተሳካ አልካዱም። ቢሆንም፣ ይህንን ጉድለት የሚሸፍን ነገር ተገኝቷል። ከተለያዩ ምንጮች ወደ ኢትዮጵያ የተላከው የውጭ ምንዛሬ ከተጠበቀው በላይ ሆኗልና። ለነገሩ፣ በየአገሩ

የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በየአመቱ የሚልኩት ገንዘብ ቀላል አይደለም። በአመት ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ እየላኩ ነው። ከኤክስፖርት ከሚገኘው ዶላር ይልቅ፣ ከዳያስፖራ የሚመጣው በልጧል። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለቤተሰብና ለዘመድ የሚልኩት ገንዘብ መጨመሩ ጥሩ ነው። ነገር ግን፣ የኤክስፖርትን ጉድለት ይሸፍናል በሚል የሚያፅናና አይደለም - በእጅጉ የሚያሳስብ እንጂ።

ከሳምንት በፊት ጠ/ሚ ኃይለማሪያም፣ በውጭ ምንዛሬ እጥረት የመንግስት ፕሮጀክቶች እንደማይስተጓጎሉ ቢገልፁም፤ ከምር ሳያሳስባቸው የቀረ አይመስለኝም። በዚያው ሳምንት የንግድ ሚኒስቴር ሃላፊዎች ከክልል መስተዳድር ተወካዮች ጋር ተሰብስበው የተነጋገሩበት ዋና ርዕሰ ጉዳይ፣ በውጭ ምንዛሬ እጥረት ነው። ወደ ውጭ የሚላኩ

Page 6: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 6 ማስታወቂያ

Page 7: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 7 ህብረተሰብ

ኤፍሬም እንዳለ

ልብ ወደ ገፅ 21 ዞሯልማስታወቂያ

የአዳማ ጉዞ ማስታወሻ!ነቢይ መኰንን

እንዴት ሰነበታችሁሳ!“እያወቀ እንዳላወቀ ሆኖ ዝም የሚል ሰው አለ።

የማያውቅ ሆኖ ዝም የሚልም አለ፣ እያወቀ ጊዜ እስኪያገኝለት የማይናገርም አለ፡፡” ይቺ አባባል ከታላቁ መጽሐፍ ላይ የተገኘች ነች፡፡

እናላችሁ…ነገርዬው ሁሉ ጭጭ ምጭጭ ያለ አይመስላችሁም! ሰዋችን ‘ዝም’ ብሏል፡፡ ታዲያማ…ዝም ማለት ግን ነገሩ ሁሉ ‘አልጋ በአልጋ’ ስለሆነ… ህይወት ‘ዓለም ዘጠኝ’ ስለሆነች… “እሰይ ስለቴ ሰመረ…” የሚባልለት ዘመን ስለመጣ ምናምን አይደለም፡፡ ሰዋችን…አለ አይደል…ዝምም ብሎ ድምጽ ሳይወጣውም፣ “ያዙኝ ለቀቁኝ” እያለ ለያዥ ለገናዥ ሳያስቸግር፣ ደረቱን ሳይደልቅ፣ ፊቱን ሳይቧጭር፣ ጸጉሩን ሳይነጭ… በሙሉ ጸጥታም “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

እንግዲህ ጨዋታም ጨዋታ ያነሳው የለ…ለምን እንደሆነ እንጃ እንጂ ምን ይመስለኛል መሰላችሁ…እዚህ አገር…አለ አይደል… ከዕድር ዳኝነትና ዕቁብ ሰብሳቢነት ጀምሮ ያሉ ‘ወንበሮች’ ሁሉ የ“እኔ ከሞትኩ…” ምናምን አይነት ሶፍትዌር የተገጠመላቸው ይመስለኛል፡፡ ልክ ነዋ… አንዳንድ ቦታ የምናየው እብሪት ቀላል ነው እንዴ! (“እኛም አንድ ሰሞን እንዲሀ አድርጎን ነበር…” የሚለው ነገር የሞባይል ‘ኮምልሰሪ ሪንግቶን’ ይሁንልንማ! የምር እኮ…አለ አይደል… “ለእኛ የተደረገውን እጥፍ ለሌላው ያድርግለት…” አይነት ነገር የሚል ‘ባለ ወንበር’ እየናፈቀን ነው፡፡ እናላችሁ…“በጥፍሬም፣ በጥርሴም ወንበሬን አላስነካም…” ባይ ሲበዛበት ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

“ልብ አድርጉልኝ…”

ክፋቱ ምን መሰላችሁ…መጀመሪያ ሲቀመጡበት ስፖንጅ በስፖንጅ የነበረው አንዳንድ ወንበር ሳይታሰብ ‘አስፈንጥሮ ሲጥል’ እንጂ ‘አስፈንጣሪ ስፕሪንግ’ እንዳለው የሚታወቀው ኋላ መሆኑ!

ደግሞላችሁ…እንግዲህ ጨዋታም አይደል… አይደለም የአገሩንና የዓለምን ታሪክ ሊያነብ…አለ አይደል…የ‘ተንኮለኛው ከበደን ታሪክ’ እንኳን የማያውቅ የእኔ ቢጤ “ፍየል ከመድረሷ…” በአገር ታሪክ ሲሳለቅ፣ እንደ ወር ወጪው የአገርን ታሪክ ቁጥር ሲቀንስና ሲያቀናንስ… ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ደምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

ሌላ ደግሞ አለላችሁ…ነገ አልመች ሲለው ትቶ ውልቅ የሚለው፣ ነገ የሚሰጠው ድርጎ ሲያንስበት ከፍ አድርጎ ድርጐ ለሚሰጥ ሌላ ጌታ ለማገለገል በጨረታው የማይገደደው…አሁን “የምናምኖች መጠራቀሚያ…” እያለ ወደሚሰደድባት አገር ‘ሽል’ ብሎ ወይ የሚነግድ ወይ ምናምኖች ሲላቸው የከረማቸውን “ፉርሽ ባትሉኝ…” የሚለው ሁሉ…አለ አይደል…“ታራለህ ትደብናለህ፣ ታዲያ ምን አባክ ትሆናለህ…” አይነት ማን አለብኝነት ኑሮውን የምድር ገሀነም ሲያደርግበት… ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

ከአንድ ጥግ አንድ ጥግ እንደ ኳስ ሲያጦዙት ከርመው…ሣር የነበረላቸው ነገር ወደ ድርቆሽ መለወጥ ሲጀምር ሽል ሲሉ… ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ

ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡እናላችሁ…እንደ ትናንትና፣ እንደ ትናንት ወዲያ

አገር “የባለ አገሯ…” መሆኗ እየቀረ እምነቱ ላይ ሲዘባበቱበት፣ የከበረ ባህሉ ላይ በ‘ግሎባላይዜሽን’ና ‘ወዳጆችን ባለማስቀየም’ ሰበብ ለሚጠየፋቸው ልማዶች እንዲጋለጥ ሲያደርጉት፣ በእሱነቱ ‘ሙድ ሲይዙበት’ (ቂ…ቂ…ቂ…)…ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

ስሙኝማ፣ እግረ መንገዴን የሆነች ነገር ትዝ አለችኝማ!…ምንም እንኳን ወደየምግብ ቤቱ በሩብ ዓመትም ቢሆን ብቅ የሚያደርግ አቅም ከጠፋ ቢከራርምም አልፎ፣ አልፎ እንደ አቅሚቲ ያለውን ተጠግቶም ቢሆን ብቅ ማለት አይቀርም፡፡ ታዲያላችሁ እዛም “ልብ አድርጉልኝ!” የሚያስብል ነገር መአት ነው፡፡

ታዲያማ…ሀሳብ አለን፣ አንዳንድ ምግብ ቤት በር ላይ የድንጋይ መፍጫ ማሽን ይቁምልንማ! አሀ…ልክ እኮ ‘ሞቶም ችኮነቱ ያልለቀቀው’ በሬ… “መንጋጋህ ይድከመው እንጂ በቀላሉማ ታፋዬን አታኝካትም…” የሚል ይመስል የሚታኘክ ሳይሆን የሚፈጭ ሥጋ እየቀረበልን ተቸገርና!

እናማ…የድንጋይ መፍጫ ‘ስታንድባይ’ ይሁንልን፡፡ ልክ ነዋ… እንደ ‘ፉድ አምቡላንስ’ ነገር ሆኖ ሊያገለግለን ይችላላ! የምር እኮ…አንዳንድ ጊዜ ከወጡ ውስጥ በመከራ ጠልፋችሁ የጎረሳችሁት

ቁራጭ ሥጋ አፋችሁ ውስጥ ሦስት መቶ ስድሳ ዲግሪ አሽከርክራችሁትም ወይ ፍንክች! “ይሄ ሥጋ ከየትኛው እንስሳ እንደተገኘ አንድዬ ይወቀው…” ብትሉ አይፈረድባችሁም፡፡ እኔ የምለው… የሀበሻ በሬዎች እንደ እኛ የሀበሻ ሰዎች ነገራቸው ሁሉ መነቸከ ማለት ነው!

ስሙኝማ…እዚህ አገር “ልብ አድርጉልኝ!” የሚያስብል ነገር እንዴት እንደበዛ የምታወቁት ምን የመሰለው ሬስቱራንት ውስጥ የምግባችሁን መቅረብ3 ተከትሎ እግራችሁ ስር የስፔንን ተዋጊ ኮርማዎች የሚያስንቅ ድመት ብቅ ብሎ ይገላምጣችኋል! “እኔ እዚህ ቅንጣቢ የሚጥልልኝ አጥቻለሁ አንተ ገንዘብ አለህና አሮስቶ ስትውጥ የድመት አምላክ አይታዘብህም!” ብሎ የሚዝትባችሁ ነው የሚመስለው፡፡…ነው ወይስ ሼፉ እንዲሰልል ልኮት ነው! ቂ…ቂ…ቂ…

ታዲያላችሁ… እንግዲህም ጨዋታም አይደል… “ቀን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል…” የሚለውን አባባል የሚያረጋግጡ፣ “ጌታዋን የተማመነች በቅሎ…” የሚለውን አባባል እውነት የሚያደርጉ፣ ላላስነጠሰው ባለስልጣንና ባለሀብት መሀረብ የሚያቀርቡ እህል እንደሚፈጅ ተምች በዙሪያው እየፈሉ ሲሄዱ… ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

በዕውቀትና በ‘ሜሪት’ ስልጣን ሳይሆን…በ‘ድርጎ ስልጣን’ ለዓይንም መከታተል በሚያስቸግር ፍጥነት ወደላይ እየተተኮሱ…የመንግሥተ ሰማያትን ዙፋን የተቆጣጠሩ ይመስል አይደለም ሌላ ሌላውን… የተፈጥሮ መብቶቹን እንኳን ሰጪና ነጣቂ ሲሆኑበት ….ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

“ይህንን ብታደርግ በዚህና በዚህ እናግዝሀለን…” ከማለት ይልቅ…“ይሄን ብታደርግ ውርድ ከራሴ…”

የአዋሳ ዕድሮችን አመራር አባላት የተሰናበትኩት ሰብሳቢው ሻምበል አህመድ ሁሴን፤ “128 ዕድሮች በጋራ እንሩጥ የተባባልነው ተሳክቶልናል፡፡ ሰውን ማጨናነቅ አልፈለግንም፡፡ ዋናው አባላቱ የዚህ ህብረት አባል ነኝ እንዲሉ ነው የፈለግነው፡፡ ተጠቃሚ መሆናቸው ቀጣዩ ጉዳይ ነው፡፡ በተጨባጭ ተጠቅመዋል፡፡ ከፍተኛ ት/ቤት፣ ከፍተኛ ወፍጮ ቤት፣ ግሮሠሪ… ብዙ የሥራ ዕድሎችን ፈጥረዋል፡፡” ሲሉኝ “መንግሥት እንዴት ያምናችኋል?” ብዬ ጠየኩ፡፡

“ከሥራችን አንፃር ነዋ! በደንብ ይከታተላልኮ! ለምሳሌ ጄክዶ ሲዳ የቤት ጥገና በጀት ሲፈቅድልን፤ በሰባቱም ክፍለ ከተማ መንግሥት በሚያውቃው ሁኔታ፣ ቀበሌም በቅርብ እያገዘን ነው ሥራውን ያካሄድነው! መንግሥትማ ምንጊዜም ከጐናችን ነው፡፡ ቦታ እየሰጠንኮ ነው ለአረጋውያን ቤት የሰራነው” አሉኝ፡፡

ልበ - ሙሉነታቸው፣ ጥንካሬና ጽናታቸው እየገረመኝ ነው ወደሚቀጥለው ጉብኝቴ ያመራሁት፡፡ ምነው ድፍን ኢትዮጵያ እንደነዚህ በጐ - ፈቃደኞች ባሰበ? የት በደረስን?/አልኩኝ በሆዴ፡፡

የእየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት እየረዳቸው የተቋቋሙ ኋላም ራሳቸውን የቻሉ፣ እስካሁን ያየኋቸው ማህበራትና ዕድሮች አራት ዋና ዋና ባሕሪ እንዳላቸው አስተውያለሁ - 1ኛ/ ሁሉም በራስ መተማመን አላቸው 2ኛ/ ሁሉም የማህበረሰቡን የልብ ትርታ በቅርብ ዳስሰው አውቀውታል 3ኛ/ ሁሉም ከመንግሥት ጋር በቅርብ ቁርኝት ይሰራሉ 4ኛ) ሁሉም የሚታይና የተጨበጠ፣ መሬት ላይ ያለ ሥራ የሠሩ ሲሆን ለዘላቂነታቸው ማረጋገጫ የሆነ ግንዛቤ አላቸው፡፡

አሁን የምሄደው ወደ “እንብራ የራስ አገዝ ቡድኖች ሕብረት” ነው፡፡

በውቅሮ ቀበሌ ምሥራቅ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ይሄ ሕብረት፤ ህፃናትና ሴቶችን እንዲሁም ወጣቶችን የሚረዳና፤ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የተቋቋሙ ቡድኖች ህብረት ነው፡፡ ቀጥሎ እምፅፍላቸው በራስ የመተማመን መልካም ምሳሌ ከምላቸው አንዱ ነው፡፡ የሕብረቱ ሰብሳቢ ታየች ብርሃኑ ናት፡፡ ከጥንካሬ ድርና ማግ የተሰራች የምትመስል ቆራጥ ሴት ናት፡፡ “ህብረቱን ‘እንብራ’ ያልነው መጀመሪያ ኑሯችን አስከፊ ነበር፡፡ እኔ ለምሳሌ ብትወስደኝ እንደመልኬ ባህሪዬም አስቀያሚ ነበር፡፡

ኑሯችን ጨለማ ነበረ፡፡ ከዛ ስንወጣ ሕብረታችንን እንብራ አልነው፡፡ በመጀመሪያ የእየሩሳሌም ድርጅት ህፃናትን ይደግፍ ነበር፡፡ በቡድን በቡድን ተደራጀን - ሃያ ሃያ ሴት ያለበት፤ 6

ቡድን ተመሠረተ፡፡ ከየቡድኑ ሁለት ሁለት ተወካይ ተውጣጣና ወደ ሕብረቱ መጣን፡፡ ሕብረቱ ያስፈለገን ለቡድኖች የገቢ ማሰባሰቢያ ዘዴ ለመፈለግ፣ የገቢ ማግኛ አመራር ለመስጠት፣ ለማደራጀት፣ የቁጠባ አገልግሎት ለመስጠት ነው፡፡ ምን ዓይነት ፈጠራ ያልክ እንደሆን፤ ለምሳሌ የሥራ ፈጠራን ለማበረታታት የምትነግድ ችሎታዋ የፈቀደውን ከሰልም፣ እንጨትም ነግዳ ራሷን እንድታቋቁም ነው፡፡ ወላጆች በተለያየ የንግድ ሙያ ሰልጥነው፣ የንግድን ትርጉም አውቀው፣ አትርፈው፣ ራሳቸውን ችለው፤ ነገ ልጆቻቸውን በራሳቸው ሙሉ አቅም እንዲያሳድጉ ነው፡፡

“ለምን ሴቶች በዙ ህብረታችሁ ውስጥ” አልኳት፤ ዙሪያዬን የከበቡኝን ከ8 ያላነሱ ሴቶች እየማተርኩ፡፡

“ሴቷ ናታ ዋንኛ የችግሩ ገፈት ቀማሽ! አሁን እኔ፣ መልክም ባይኖር፤ ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው የምታየኝ፡፡ ፊት ግን በጣም አሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ ነበር ያለሁት! ሁላችንም ችግር ውስጥ ነበርን፡፡ ባህሪያችንም እንደዚያው፡፡

ይሄ ባህሪ እንዲለወጥ መስዋዕትነትን ከፍሎ እየሩሣሌም መጀመሪያ ቤት ለቤት በመዞር የእኛ ባህሪ እንዲለወጥ ነው ያደረገው፡፡ የሥራ ባህል እንድናዳብር፣ የጠባቂነት መንፈስ ከእኛ እንዲርቅ ነው የሠራው፡፡ የእኛን ባህሪ መለወጥ አቅጣጫ ሲያይ፤ የፕሮጀክት ሥልጠና ሰጠን፡፡ የልምድ ልውውጥ እንድናደርግ አደረገን፡፡ ድልድያችን ሆነ! ከዚያ ፕሮጀክት ቀረጽን! ምን ትፈልጋለህ”

“ከዚያስ እንዳሰባችሁት ምላሽ ተገኘ?” አልኳት፤ ባላቋርጣት እየተመኘሁ፡፡

“ወይ ጉድ! ከፍትፍቱ ፊቱኮ ነው! ማንም ሰው የሚጠቅም ነገር ለማግኘት አበረታች መልክ ካገኘ ይለወጣል፡፡ ደብረማርቆስ ሄደን የልምድ ልውውጥ አድርገናል፡፡ ከዚያ ባገኘነው ዕውቀት አርባ የቡድን አባላትን ሰበሰብን፡፡ አባላቱ የገቢ ማስገኛ ሥልጠና ሠለጠኑና የፈጠራ ሥራ መሥራት ጀመሩ፡፡ ከዚያ የችግሩን ስፋት ጠልቆ እንዲያውቀው፣ መንግሥት የሴቷን ድምጽ እንዲሰማ ክለባት አቋቋምን፡፡ ከሃይማኖት ከሴት ከወጣት…ሁሉን አቀፍ ፕሮጄክት ቀረጽን፡፡ በጀት ፀደቀልን፡፡ ማገዶ ቆጣቢ ሠራን፡፡ አነስተኛ ምግብ ቤት ከፈትን፡፡ ራሳቸውን አሠልጣኝ ሆኑ - ሠልጣኞቹ፡፡ ሙዚቃ የሚማሩ እዚህ የምታያቸው ህፃናት አሉ፡፡

“ጄክዶን እንዴት ታዩታላችሁ?” “እየሩሳሌም (ጄክዶ) እንዲሁ ልታይ ልታይ የሚል

ድርጅት ቢሆን ኖሮ እኛም አናምንበትም፤ አንለወጥም ነበር፡፡ ሴቷ ላይ ትኩረት ስለሚያደርግና ክትትል ስለሚያደርግ ነው ውጤት ያመጣው፡፡ እኛ ባሁኑ ሰዓት ትልቅ ተደማጭነት የአለን ነን”

“መለወጥ ስትይ እንዴት ነው?” አልኩ አሁንም

አቋርጪያት፡፡ “አየህ፤ ዱሮ ራሳችንን ገለን እርዳታ ጠባቂ ሆነን፤ ማዳበሪያና

የዘይት ጀሪካን ይዘን ነበር የምንሮጠው፡፡ ዛሬ እንታገል፣ እንሻሻል፣ እንለወጥ፤ አልፈን ተርፈንም የተበደለችዋን ሴት፣ የተበደለችውን ሕፃን ፍትሕ እንድታገኝ እናድርግ እያልን ነው፡፡

“መንግሥት አይደግፍም የሚል ሃሳብ ያላቸው አንዳንድ ወገኖች አሉ፡፡ ለምን ይመስልሻል?”

“መንግሥት ያስፈልጋላ! አለመፍራት ተደጋግፈን እንሥራ ለማለት አለመፍራት ህብረተሰቡ ጋ ተደራሽ ለመሆን መንግሥት ያግዛል፡፡ እኛም የመንግሥትን ሥራኮ ነው የምንሠራው! ክፍተት ካለ እንሞላለን፡፡ አንዴ እዚህ ሥራ ውስጥ ከተገባ የነብር ጭራ እንደመያዝ ነው! ህፃናት ሲደፈሩምኮ እዚህ ድረስ መጥተው ውሰጂን ፖሊስ ጣቢያ ይላሉ፡፡ ማደሪያ እንደሰጣቸዋለን፡፡ ፍትሕ እንዲያገኙ እንከታላለን፡፡

ነገ መለወጥ አለበት፡፡ የጠባቂነት መንፈስ አገር ያሽመደምዳል፤ እንክርዳድ የበላ ሰው ነው የሚያደርገው”

እየገረመችኝ፤ ፊቴን ወደ ሌሎቹ የአመራሩ አባላት መለስኩ፡፡ ተራ በተራ

ጠየኳቸው “መመልመያ መስፈርታችሁ ምንድን ነው?” አልኩ፡፡ “አባት እናት የሞተበት፣ አባት ወይ እናት የሞተበት፣ እናት

አባት እያላቸው መማር ያቃታቸው፣ ዋናው መስፈርታችን ዞሮ ዞሮ ችግር ነው” አለችኝ አንዷ፡፡

“25 ወጣቶች ወደኛ መጥተው ጄክዶ ሲዳ በለቀቀልን በጀት የሊስትሮ ዕቃ ገዝተን አሁን ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሰዋል” ቀጠለች ሌላዋ፡፡

“አንዱን ወጣት አባል አንተስ ምን ትለኛለህ?” አልኩት፡“ብርሃንና ንጋት የእንጨትና የብረት ሥራ ማህበር ነው

የእኛ” አለ፡፡ (ስማቸው ተስፋን ያዘለ መሆኑ በሆዴ አስገርሞኛል - ብርሃን ይወዳሉ) “በክፍለ ከተማው በጥቃቅንና አነስተኛ 10 ልጆች ተደራጀን፡፡ ትምህርት ጨርሰው ሥራ ያላገኙና ትምህርት አቋርጠው እቤት ቁጭ ያሉ ናቸው - ሙያ እያላቸው የመሥራት ዕድሉን ያጡ ናቸው፡፡ መሬት፣ ከነቤቱ፣ ከነማሽኑ ሰጠን ክፍለ ከተማው - ቀጠልን መንቀሳቀሻ ገንዘብ ፍለጋ ተሰማራን፡፡

አቶ ማስረሻ የእየሩሳሌም የአዋሳ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ፤ “ገንዘብ መለመን የለባችሁም፡፡ በራሳችሁ

ተፍጨርጭራችሁ መንቀሳቀስ አለባችሁ” ብለው የመከሩንን መቼም አንረሳውም፡፡ ከኪሣችን መቶ መቶ ብር አዋጥተን በ1000 ብር ዝም ብለን ሥራ ጀመርን፡፡ አሁን ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለነው…ከእንብራ መጠናከሪያ አግኝተናል - እንደማህበራችን ነው እምናየው፡፡ ወጣት ፈጣን ነው፡፡ ብዙ ኢንፎርሜሽን ያገኛል ያንን እንጋራለን፡፡ ወደፊት ብሎኬት ሥራ፣ ሻይ ቡና፣ ዶሮ እርባታ ወዘተ እቅድ አለን፡፡

ባንዱ ብንከስር ባንዱ እንካሳለን፡፡ እንጠነክራለን ምክንያቱም እንብራም፣ የእየሩሳሌም ድርጅትም፤ ከጐናችን አሉ” አለኝ፡፡

አዛለች ንዳ የህብረቱ ፀሐፊ ስለራሷ ስትነግረኝ እንባ እየተናነቃት ነው - “ማንም ሰው አያቀኝም ነበረ፡፡ ልጆቼ አጉል ቦታ ነበሩ፡፡ ባሌ ሞቷል፡፡ ጥሩ ሁኔታ ላይ አልነበርኩም (አለቀሰች) እንዴት ሆኖ እንዳገኙኝ እግዜር ነው የሚያውቀው፡፡ ተደብቄ የነበርኩትን ሴትዮ ጐትቶ አወጣኝ…መልምለው ያወጡኝ እህቶቼ ነይ አሉኝ… የምክር አገልግሎት ሰጡኝ፤ ሰው አረጉኝ! አደለም በትርፍ ሰዓት በሥራ ሰዓቴም እየመጣሁ ማህበሩን አገለግላለሁ፡፡ ራዕያችን ሩቅ ነው” አለች፤ በጣም ሆድ ታባባለች፡፡

“አባቴ ሞቷል” ታላቅ ወንድማችን እኛን ለማሳደግ ትምህርት ትቶ የቀን ሥራ ገብቷል ጄክዶ መጥቶ ቤት ለቤት መለመለን፡፡ ት/ቤት ገባሁ፡፡ አሁን ተመርቄ ሥራ ይዣለሁ፡፡ እናቴም በራስ ገዝ ተደራጅታ ተዘዋዋሪ ብድር ወስዳ ትነግድም ነበር፡፡ አሁን ጥሩ ሆነናል፡፡ ለማህበሩ በበጐ ፈቃድ እያገለገልኩ እገኛለሁ” አለኝ ሌላው ወጣት፡፡

ወደ አንዷ ዞር ብዬ “ምን አገኘሁበት ትያለሽ ይሄን ህብረት?” አልኳት፡፡ በአጭሩና በሚገርም ዓረፍተነገር ነው የመለሰችልኝ - “በራስ መተማመንና ተስፋ” አለችኝ፡፡ አጨብጭቡላት ልል ምንም አልቀረኝ፡፡

“እነጄክዶ ሲሄዱ ምን ይውጣችኋል?” አልኩ፤ ሁሉንም አንዴ ቃኝቼ፡፡

አንዷ ተሻምታ መለሰችልኝ “ትቀልዳለህ? ጄክዶ ባመቻቸው መንገድ ላይ የገቢ

ማስገኛዎችን ፈጥረናል፡፡ እየተጠናከርንኮ ነው! እንብራ 3 ባጃጅ አለው፡፡ ሸማች አለው፡፡ የዳቦ ቤት ሊጀምር ነው፤ በዛ ላይ ህብረተሰቡ እርስ በርሱ እንዲደጋገፍ፣ የጠባቂነት መንፈስ እንዲጠፋ፤ ብዙ ሥራ ሠርተናል፡፡ ያ የዘላቂነት ሀብታችን ነው፡፡ ምንም አንጨነቅም - ራሳችንን ችለናል፡፡”

በመጨረሻ ምንም ወዳልተናገረችው ሴት ዞሬ፤ “ለመሆኑ በሥራው ላይ ትጣላላችሁ” አልኳት፡፡ ሁሉም

ፈገግ አሉ፡፡ “ለምን እንጣላለን” አለችና፤ ቆየት ብላ “አሃ ብንጣላም

እዛው እንታረቃለን” አለችና ሁላችንንም አሳቀችን፡፡ ይሄ ሁሉ ውይይት ደጅ ሣሩ ላይ ክብ ሠርተን

ያወራነው ነበር፡፡ ቢሮ ገብቼ ፎቶዎቹንና ቻርቶቹን አይቼ ተሰናበትኳቸው፡፡

ነገ ወደ ሻሸመኔ - አጄ መሄዴ ነው፡፡ ፊቴን ወደ አጄ አዙሬ ተኛሁ!!

* * *(ጉዞዬ ይቀጥላል)

“የጠባቂነት መንፈስ አገርን ያሽመደምዳል፡፡ እንክርዳድ የበላ ሰው ነው እሚያረገው”

Page 8: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 8

ኤልያስ

ፖለቲካ በፈገግታ

መበልፀግ የሚፈልጉ

ብቻ የሚያነቡት

የስኬት መፅሃፍ!!

በየመፃህፍት ቤቱ

ያገኙታል!!

የድርጅታችን ማህተም መጥፋቱን እና ለውጥ መደረጉን ስለማሳወቅ

ድርጅታችን እስኩል ኦፍ ቱሞሮ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ከዚህ ቀደም ስንጠቀምበት የነበረው ሞላላ ቅርጽ ያለውና ማህተም የጠፋብን ስለሆነ ከሰኞ 11/2/2006 ዓ.ም ጀምሮ የማያገለግል መሆኑን እና በሌላ ዓይነት ማህተም መቀየራችንን እንገልፃለን፡፡

ከአክብሮት ሠላምታ ጋር

SCHOOL OF TOMORROW P.L.Cእስኩል ኦፍ ቱሞሮ ኃ.የ.የግ.ማኅ

እኔ የምለው … ባለፈው እሁድ ብሄራዊ ቡድናችን ብሔራዊ ኩራት አጐናፀፈን አይደል! (የልማት ውጤት እኮ ነው!) እውነቴን ነው የምላችሁ…

ዋልያዎቹ ብርቅዬነታቸውን ለዓለም አሳይተዋል። በቴክኒክ ችግር 2ለ1 በሆነ ውጤት ቢሸነፍም እንዳሸነፈ እንቆጥረዋለን፡፡ የደጋፊውንም የጨዋነት ብቃት ሳናደንቅ አናልፍም፡፡ አንዳንድ ደጋፊዎች ግን አውቀውም ይሁን ሳያውቁ የ “ማሪዋና” ቅጠል የታተመበት ባንዲራ ጭንቅላታቸው ላይ ሸብ አድርገው ታይተዋል-በኢቴቪ መስኮት ሳይቀር፡፡ (ይሄኔ ነው መሸሽ) አንዳንዶች ምን ቢሉ ጥሩ ነው? የአባባ ጃንሆይ ባንዲራ (የሞአንበሳ ምስል ያለበት) ማረን ብለዋል (ማስጠየቁ ባይቀርም) አሁንም ከስቴዲየም ወጥተን ፓርላማ እንግባ፡፡ ጠ/ሚኒስትሩ ባለፈው ሳምንት በአዲሱ ፕሬዚዳንት ንግግር ላይ ለፓርላማ የሰጡትን ማብራሪያ ተከታትላችኋል? ንዴት የማይነካቸው ጠ/ሚኒስትር ሰጥቶናል እንጂ በፓርላማ የመድረክ ተወካይ ስንት ጭርጭርር….የሚያደርግ ውንጀላ ሰንዝረዋል - በጠ/ሚኒስትሩ ላይ ሳይሆን በመንግስትና በኢህአዴግ ላይ፡፡ ዳያስፖራው በ40/60 የመንግስት ቤቶች ፕሮግራም ተጠቃሚ እንዲሆን የተደረገው፣ መንግስት የውጭ ምንዛሬ ለመሰብሰብና ዳያስፖራውን በአባልነት ለመያዝ ነው ሲሉ አቶ ግርማ የወንጀሉ ሲሆን ጠ/ሚኒስትሩ ግን ተረጋግተው ከእውነት የራቀ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ኢህአዴግ ከዳያስፖራው ድምፅ (የምርጫ ማለታቸው ነው) አያገኝም ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ፤ ከዳያስፖራ የገንዘብ ድጋፍ ተቀብሎ እንደማያውቅም አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ (ኢህአዴግ እኮ ቀጭን ጌታ ነው!)

ይሄ ደግሞ እውነት መሆኑን ቅንጣት አልጠራጠርም፡፡ እንዴ 7 ሚ. አባላት ያቀፈ ግዙፍ ፓርቲ ለምን ብሎ ከዳያስፖራ ገንዘብ ይለምናል፡፡ (በደህና ቀን ተቃዋሚ ፓርቲ ከመሆን ወጥቷል!) በዚያ ላይ በሽ የቢዝነስ ተቋማት አሉት (“ኢንዶውመንት” ነው የሚላቸው?) በነገራችሁ ላይ ኢህአዴግ ራሱን “አውራ ፓርቲ” ቢልም እኮ ያምርበታል፡፡ ትልቅ ሥልጣን (Power) ብቻ ሳይሆን ትልቅ ካፒታልም ያለው ፓርቲ እኮ ነው! እኔ ተቃዋሚ ፓርቲ ብሆን ኖሮ “ህልምህ ምንድነው? ስባል ምን እንደምል ታውቃላችሁ? “ህልሜ ኢህአዴግን መሆን ነው!” ባይናገሩትም እኮ የሁሉም ተቃዋሚ ፓርቲዎች ህልም ይሄው ነው፡፡ “ወፈ ሰማይ አባላት” ያሉት ገዢ ፓርቲ መሆን! ወዳጆቼ… “ህዝቡን የስልጣን ባለቤት

ለልማት የሚከፈለው መስዋዕትነት በ“ደብል ዲጂት” መቀነስ አለበት!ልማትና ትዕግስት ያላቸው ቁርኝት ዘንድሮ ገባኝ!

ዲሞክራሲያችን በስንት ዲጂት እንዳደገ ይነገረን!

ማድረግ” ምናምን… የሚለው የተበላ ዕቁብ ነው!! በ2000 ዓ.ም የኢህአዴግ ካፒታል

ከ1200ሚሊዮን ብር በላይ ነበር አሉ፡፡ (ከተሳሳትኩ እታረማለሁ!) እኔ የምላችሁ … ከአነስተኛና ጥቃቅን የብድር ተቋማት፣ ገንዘብ ተበድረው ወደ ደቡብ አፍሪካ የገቡ ወጣቶች እንዳሉ ሰምታችኋል? የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ፤ ፓርላማ ውስጥ ሲናገሩ ሰምቼ እኮ ነው፡፡

ለነገሩ ጠ/ሚኒስትሩም ቢሆኑ ለማስተባበል አልሞከሩም፡፡ “ከስንዴ መሃል እንዳክርዳድ አይጠፋም” ዓይነት መልስ ነው የሰጡት፡፡ መፍትሄውም ስንዴውን ሁሉ መድፋት ሳይሆን እንክርዳዱን ለቅሞ ማውጣት ነው ብለዋል - የተከበሩ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፡፡

በፓርላማ ብቸኛው የተቃዋሚ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ፤ ተቃዋሚዎችና መንግስት ዓይን ያወጣ የእርስ በርስ መፈራረጅ አቁመው፣ የርዕዮተ ዓለም ልዩነታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ በሚያግባባቸው አገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት አለባቸው ሲሉም አቋማቸውን ገልፀው ነበር (የተሰናባቹ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ምክር ትዝ አለኝ!) ጠ/ሚኒስትሩ ግን ይሄ የተዋጠላቸው አይመስሉም። በእርግጥ “የተቃዋሚዎች መኖር ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ብቻ ሳይሆን ለገዢው ፓርቲም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል” በማለት ነው መልስ መስጠት የጀመሩት፡፡ ከዚያ ግን አመረሩ (ፊታቸው ላይ ምሬት ባይታይም!) “ሌት ተቀን የጐዳና ላይ ነውጥ አድርጌ መንግስት እለውጣለሁ” ከሚል ተቃዋሚ ጋር እንዴት ነው በጋራ መስራት የምንችለው?” በማለት ምላሽ ሰጡ፤ ጠ/ሚኒስትሩ። እኔ የምላችሁ ግን… “ነውጥ” ከ97ቱ ምርጫ ጋር “ታሪክ” አልሆነም እንዴ? እኔ እኮ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተቃዋሚዎች የሚያደርጉት ሰላማዊ ሰልፍ፤ ህጋዊና ሰላማዊ ይመስለኝ ነበር። ደግሞም አይፈረድብኝም … ህጋዊ ፓርቲዎች ናቸው፡፡ የሰላማዊ ሰልፍ ፈቃድ አላቸው፡፡ ፖሊስ ጥበቃ ያደርግላቸዋል፡፡ እንዴት “ነውጠኞች” ብዬ ልጠርጥር?

መንግስት ባለሃብቱን ሁሉ “ኪራይ ሰብሳቢ” ይላል በሚል ለቀረበው ውንጀላ መልስ የሰጡት ጠ/ሚኒስትሩ፤ “ኪራይ ሰብሳቢ” የሚለውን ቃል በትክክል ካለመረዳት የመጣ ስህተት ነው ብለዋል- በሰሞኑ የፓርላማ ውይይት፡፡ በ”ነውጥ” ጉዳይ ላይም ብዥታ (የኢህአዴግን ቋንቋ ተውሼ ነው!) ያለ ይመስለኛል፡፡

እናላችሁ … በሰላማዊ ሰልፍና በነውጥ መካከል ስላለው ልዩነት ጥልቅ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ዎርክሾፕ ነገር ያስፈልገናል፡፡ (ለእኛም፣ ለኢህአዴግም፣ ለተቃዋሚም)

በቀደም በፓርላማ ጠ/ሚኒስትሩ፤ የአገሪቱ ኢኮኖሚ ለ10 ተከታታይ ዓመት በሁለት ዲጂት ማደጉን ሲናገሩ ሰምቻለሁ፡፡ (ኒዮሊበራሎችም በግዳቸው አምነዋል!) አሁን የእኔ ጥያቄ ምን መሰላችሁ? የአገሪቱ ዲሞክራሲ ማደግና መውደቁን

የሚነግረን ማነው? የሚል ነው፡፡ (በዲጂት ማለቴ ነው!) ከምሬ ነው… ዲሞክራሲያችን በስንት ዲጂት እንዳደገ እንዲነገረን እንፈልጋለን። (እንደኢኮኖሚው ባለሁለት ዲጂት አስመዝግቦ ይሆናል እኮ!) ነገሩን እኛ ሳናውቀው ቀርተን እኮ አይደለም፡፡ ለወዳጅም ለጠላትም ግን በፐርሰንት ተሰልቶ ሲነገር ደስ ይላል። (ዲሞክራሲ በፐርሰንት ይለካል እንዴ?)

መቼም ጉዳችን አያልቅም አይደል? የመብራት፣ የውሃ፣ የኔትዎርክ፣ የታክሲ መጥፋት ወዘተ… አንሶን ሰሞኑን ደግሞ የዳቦ እጥረት ተከስቷል - በስንዴ መጥፋት፡፡ እናላችሁ… ሌላ የዳቦ ሰልፍ እንዳይጀመር ክፉኛ ሰግቻለሁ፡፡ (እንደታክሲው!)

Daily Express የተባለው ጋዜጣ April 17 ቀን 1933 ዓ.ም ባወጣው ዘገባ፤ በሶቭየት ህብረት በአንድ አርብ ቀን ብቻ 7ሺ ሩሲያውያን ለዳቦ ተሰልፈው እንደነበር ጽፏል፡፡ (ሰልፍና ሶሻሊዝም ተለያይተው አያውቁም!) እናላችሁ… ከእንዲህ ዓይነቱ መዓት እንዲሰውረን ሱባኤ መግባት ሳይኖርብን አይቀርም። (ሱባኤ ለመግባት የግድ 7ሺ ሰው ለዳቦ መሰለፍ አለበት እንዴ?)

ባለፈው ሳምንት የገጠመኝን ደግሞ ላውጋችሁ፡፡ እንደአጋጣሚ ካዛንቺስ አካባቢ መብራት ስላልጠፋ (አንዲት ማታ እኮ ነው!) ኢቴቪ በትራንስፖርት እጥረት ዙሪያ የሰራውን ዘገባ እየኮመኮምኩ ነበር። መፍትሔ ይመጣል የሚል ተስፋ አድሮብኝ እንዳይመስላችሁ፡፡ ሥራ ከምፈታ ብዬ ነው፡፡ የዛን ዕለት ማታና አንድ ሌላ ቀን ሁለት የካድሬ ቅላፄ ያላቸው የታክሲ ተራ አስከባሪዎች የሰጡት ድፍረት የተሞላበት አስተያየት ግርም ብሎኛል፡፡ ሁለቱም ሴቶች ናቸው፡፡ ሁለቱም ከአፋቸው ነጠቅ ነጠቅ ያደርጋቸዋል፡፡ ሁለቱም እየተቆጡ ነው የሚናገሩት። ተራ የማስከበር ሥራ ሳይሆን የአዲስ አበባን ነዋሪ ሥነምግባር የማስተማር ሃላፊነት የተጣለባቸው ይመስላሉ፡፡ በስራ ሰዓት መግቢያና መውጪያ ላይ ስለሚፈጠረው የትራንስፖርት እጥረት ነበር የሚናገሩት፡፡ “ህዝቡ…ቅጥቅጦች ላይ አይሳፈርም…ሁሉም ቆሞ ሚኒባስ (ታክሲ) ነው የሚጠብቀው፤ ይሄ ተገቢ አይደለም” አሉ፡፡ ወቀሳቸው አላበቃም “ህብረተሰቡ ለምን ማልዶ ተነስቶ ወደ ስራው አይሄድም? ሁሉም 2 ሰዓት ስለሚመጣ እኮ ነው ችግር የሚፈጠረው” አሁንም በቁጣ! አንደኛዋ ይባስ

ብላ፣ል ሰራተኛው ጠዋት አንድ ሰዓት ቀደም ብሎ ስራ እንዲገባ፣ ማታም እንዲሁ ከስራው አንድ ሰዓት ቀደም ብሎ እንዲወጣ በፓርላማ ያልፀደቀ መመሪያ አወጣችልን፡፡

ለታክሲዎች እያቆራረጡ መጫንና ለታሪፍ ጭማሪም ተጠያቂው ህብረተሰቡ ነው ስትል ደመደመች፡፡ (አዲስ አበቤ ፈረደበት!) “ህዝቡ ራሱ እኮ ነው፤ መብቱን አያስከብርም!” አለች - ብላ፡፡

ይሄኔ አንድ ነገር ተጠራጠርኩ፡፡ ተራ አስከባሪዋ “ፒፕሉ” ላይ ቂም ሳይኖራት አይቀርም፡፡ ወይም ደግሞ “ይሄን ህዝብ ውረጂበት!” ብሎ የላካት “የውጭ ኃይል” አለ - አልኩ ለራሴ፡፡ በኋላ ላይ “እንተዋወቃለን እንዴ?” ልላት ሁላ ዳድቶኝ ነበር -በአካል አጠገቤ ያለች መስላኝ፡፡ የምትናገረው በኢቴቪ መስኮት መሆኑ ትዝ ሲለኝ በራሴ ላይ ከት ብዬ ሳቅሁኝ፡፡ (በራስ መሳቅ ጤንነት ነው ተብሏል!)

አይገርምም…በትራንስፖርት እጥረት ጠዋት ማታ የምንሰቃየው አንሶ ቤታችን ድረስ በኢቴቪ በኩል እየመጡ እንዲሁ ሲሞልጩን! ወደዘገባው መቋጫ ላይ ጋዜጠኛው ያነጋገራቸው የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ ትንሽ ይሻላሉ፡፡ ህብረተሰቡ ለልማት የከፈለውን መስዋዕትነትና ታጋሽነት አድንቀዋል፡፡ (ሃበሻ እኮ በትዕግስት አይታማም!) የትራንስፖርት ችግሩን በተመለከተ ግን አንዳችም የመፍትሔ ሃሳብ አልሰነዘሩም፡፡ “በትዕግስታችሁ ግፉበት!” ከማለት በቀር፡፡

በነገራችሁ ላይ ልማትና ትዕግስት ያላቸውን ተፈጥሮአዊ ቁርኝት በደንብ የተረዳሁት ዘንድሮ ነው፡፡ አንዳንዴ ሳስበው ግን እዚህች መዲናችን ላይ ለልማት የሚከፈለው መስዋዕትነት ልኩን ያለፈ ይመስለኛል፡፡ (ግን መስዋዕትነት ያስፈልጋል እንዴ?) አያችሁ… አንዳንዱ መስዋዕትነት ለመንግስት ሹመኞች ስንፈት የምንከፍለው ነው። ሁሉም እየተነሳ ችግሩንና ድክመቱን በልማቱ ሲያሳብብ አያበግንም?

የሰለጠኑት አገራት እኮ እንኳን ለልማት ለጦርነት የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመቀነስ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡ ሰው አልባ ተዋጊ ጄቶችን ለምን የፈጠሩ ይመስላችኋል? መስዋዕትነትን በ “ደብል ዲጂት” ለመቀነስ እኮ ነው! እኛም የልማት መስዋዕትነታችንን በ “ደብል ዲጂት” መቀነስ አለብን!! (ሞትን እኮ!)

Page 9: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 9 ህብረተሰብ

ቱሪስት ወደ ገፅ 24 ዞሯል

ፈረንሳይ ከሌላው ሀገር የተለየ ቅርስ ወይም የተፈጥሮ መስሕብ የላትም፡፡ ነገር ግን ከሕዝብ ቁጥሯ በሚሊዮኖች የላቀ ቱሪስት በየዓመቱ

ይጎበኛታል፡፡ ጎረቤቷ ጣሊያን ከፈረንሳይ በቁጥር የበለጡ ዓለምአቀፍ ቅርሶች ብታስመዘግብም እንደ ፈረንሳይ አልጎረፈላትም፡፡

ኢትዮጵያም ዓለም አቀፍ ቅርስ በማስመዝገብ ከአፍሪካ አንደኛ ናት - ዘጠኝ ቅርሶች በማስመዝገብ። ስምንት ስምንት ቅርሶች በማስመዝገብ የሚከተሏት ደቡብ አፍሪካ፣ ቱኒዚያ እና ሞሮኮ ናቸው። ጎረቤት ኬንያ ደግሞ አራት ቅርሶች ብቻ ነው ያስመዘገበችው፡፡

እ.ኤ.አ በ2007 ይፋ የተደረገውን ሃምሳ ምርጥ የዓለማችን ቱሪስት መዳረሻ ሀገሮች ዝርዝርን ስንመለከት ከአፍሪካ ግብጽ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሞሮኮና ቱኒዚያ ነበሩ የተካተቱት፡፡ ግብፅ 8.6 ሚሊዮን ቱሪስቶች ስታስመዘግብ ቱኒዝያ 6.5 ሚሊዮን አስመዝግባለች፡፡ በእርግጥ ባለፉት ሦስት አመታት ከተከሰተው የአረብ አብዮት ጋር ተያይዞ የቱሪስቶች ቁጥር ማሽቆልቆሉ አልቀረም፡፡ አገራቱ ሲረጋጉ ግን እንደገና ቁጥሩ አድጓል፡፡ በኢትዮጵያ ደግሞ በ2002 ዓ.ም የተመዘገበው የቱሪስት ቁጥር ግማሽ ሚሊዮን እንኳን አልደረሰም - 468,365 ነው፡፡ የባሕልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከስድስት ዓመት በኋላ በ2012 ዓ.ም ኢትዮጵያን ከአፍሪካ አምስት ምርጥ የቱሪስት መዳረሻ ሀገራት አንዷ

መልካሙ ተክሌ ([email protected])

“ምርጥ የቱሪስት መዳረሻ” የመሆን ህልማችን ይሳካ ይሆን?

ለማድረግ አቅዷል፡፡ ሆኖም እቅዱ ከእነቱኒዝያ፣ ታንዛንያ እና ኬንያ አንጻር ሲታይ ገና እጅግ በጣም ብዙ ይቀረዋል፡፡

በሌላ በኩል መንግስት ተጨማሪ ሰባት ቅርሶች በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በእንቅስቃሴ ላይ ነው፡፡ ከቅርሶቹም መካከል የመስቀል በአል እና ባሕረሐሳብ የተሰኘው የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ይገኙበታል፡፡ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በደን ምንጠራና በሌላ የሰዎች ተጽዕኖ ከዓለም ቅርስነት የመፋቅ አደጋ አንዣቦበት እንደነበር ይታወቃል፡፡ ፓርኩን የመከለል እንቅስቃሴ በመጀመሩ ነው ከመሰረዝ የዳነው፡፡

የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማስፋፋት

መንግሥት ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ አምስት ክፍሎች ያሉት ብሔራዊ የቱሪዝም ልማት ፖሊሲ አዘጋጅቷል፡፡ የፖሊሲው ክፍል ሦስት፣ ቁጥር አራት “በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ገበያ ፉክክር ውስጥ ብቁ ተወዳዳሪ ለመሆን የማስተዋወቅ ሥራን በመሥራት ጠንካራ የገበያ ትሥሥር” መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ያወሳል፡፡ ተገቢ የፕሮሞሽን ሥራዎችን መስራት አስፈላጊ እንደሆነ ይጠቁማል - ፖሊሲው። በዚህም መሠረት የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር፤ ዓለም አቀፍ ዐውደርእዮችን እንደ ዋነኛ የቅስቀሳ ዘዴ እየተጠቀመባቸው ይገኛል፡፡ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ሥራዬ ብሎ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ቅርሶችንም ሆነ የተፈጥሮ መስህቦችን ሲያስተዋውቅ

አይታይም፡፡ መገናኛ ብዙሃኑ በራሳቸው ጊዜ መጥተው ስለ ቅርሶቹና መስሕቦቹ ከሚዘግቡት በቀር በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ለምን መስህቦችን አታስተዋውቁም በሚል የተጠየቁት በሚኒስቴሩ የሕዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አወቀ ጤናው፤ “በዚህ መልኩ አናስተዋውቅም፡፡ ከዚያ ይልቅ በምናተኩርባቸው ሀገራት ያሉ ታዋቂ ፀሐፍትንና ሌሎች ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎችን በመጋበዝ ስለ ኢትዮጵያ ቅርሶችና መስሕቦች እንዲጽፉ፣ እንዲናገሩ እናደርጋለን፡፡ በዓለም አቀፍ ዐውደርእዮች በመሳተፍም ሀገራችንን ይበልጥ እናስተዋውቃለን” ሲሉ መልሰዋል፡፡

በቱሪዝም ዘርፉ እንደ ድክመት ከሚጠቀሱ ጉዳዮች አንዱ በዘርፉ የሰለጠኑና የተካኑ ባለሙያዎች በበቂ ሁኔታ አለመኖር ነው፡፡ አቶ አወቀ በበኩላቸው፤ ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር በዘርፉ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎችን መድቦ እየሰሩ መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡

አቶ አብዱ ከድር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

ማስታወቂያ

Adress around flamingo area tomi tower ground and 4Th floor

አድራሻ - ፍላሚንጐ አካባቢ ቶሚ ታወር ህንፃ ላይ Ground & 4th floor እንገኛለን፡፡ በመጀመሪያው ወለል ላይና 4ኛ ፎቅ ላይ

New Arrival ቦሌ ፈርኒቸርmake us your choice and see the difference

ውበት፣ ጥራት እና ምቾት ያላቸውን የቤት እና የቢሮ ዕቃዎች ከውጪ ሀገር በማስመጣት በተመጣጣኝና በሚስማማዎ ዋጋ አቅርበንልዎታል፡፡

ይሙጡና ይጐብኙንበምርጫዎ ይደሰታሉ

ስልክ 0924-37-2904/0115-585015/26

Page 10: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 10

መንግስት ወደ ገፅ 24 ዞሯል

ህብረተሰብ

ደረጀ ኅብስቱ [email protected]

ማስታወቂያ

የDV 2015 ማመልከቻ ጊዜ ከመስከረም 21 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 23/2006 ዓ.ም በመሆኑ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ የአገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች አገልግሎቱን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እየገለፀ የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይጋብዛል፡፡

ያስታውሱየቆይታ ጊዜው ለአንድ ወር ብቻ በመሆኑ በአስቸኳይ

ፎርሙን በመሙላት ይላኩልን፡፡ እኛ በኢንተርኔት እናስተላልፍልዎታለን፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ በድርጅቱ አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች የተለጠፉትን ማስታወቂያዎች ይመልከቱ፡፡

በኢትዮጵያ ፖስታለአንድ ወር ብቻ

DV 2015

መልካም እድልየኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት

ተስፋዬ ድረሴ “ጋ” ቦታን፣ አካባቢን፣ መድረሻን (አቅጣጫን)

እና አድራሻን አመልካች ቃል ነው፡፡ “እዚህ ጋ…” ማለት እዚህ ቦታ ማለት ነው፡፡ አንድ ሰው “ሰዓቴ የወደቀው እዚህ ጋ ነው” ካለ “እዚህ የምታዩት ቦታ፤ መሬት ወይም የሆነ ቁሳቁስ ላይ ነው” ማለቱ ነው። ጋዜጠኞች “እዚህ ጋ አንድ ጉዳይ እናንሳ” ሲሉ አሁን እያነበብን ወይም እየተናገርን የደረስንበት “ቦታ” (ቆም ብለን) ማለታቸው ነው፡፡ “አደባባዩ ጋ…” እንገናኝ ያለን ሰው የምንገናኝበትን አካባቢ ወይም ቦታ እየጠቆመን ነው፡፡ “ወንድሜ ጋ መሄዴ ነው” ያለችን ሴት የምትጓዝበትን አቅጣጫ ወይም መድረሻዋን እየነገረችን ነው፡፡ እስከ አስር ሰዓት ድረስ “ወንድሜ ጋ እቆያለሁ” ካለችን እስከዚያን ሰዓት ድረስ መገኛ አድራሻዬ እዚያው ወንድሜ ዘንድ (ጋ) ነው ማለቷ ይሆናል፡፡ ወንድሟን ልታገኘው ወይም ላታገኘው ትችላለች፡፡

“ጋር” አብሮ መሆንን፣ አብሮ መገኘትን የሚገልጽ ቃል ነው፡፡ “ጋር” ብቻውን አይቆምም፤ “ከ”ን አስቀድሞ “ከ…ጋር” ሲሆን ነው ትክክል የሚሆነው፡፡ “ጋር” ቦታን፣ አካባቢን፣ አቅጣጫን፣ መድረሻን እና አድራሻን አያመለክትም፡፡

“እዚህ ጋር አንድ ነጥብ እናንሳ…” ያለ ጋዜጠኛ የሰራው ዓረፍተ ነገር ብላሽ ነው፡፡ ትርጉምም አይሰጥም፡፡ ጋዜጠኛው “አሁን የደረስንበት ቦታ ላይ ሆነን” ለማለት ፈልጐ ከሆነ መጠቀም ያለበት “ጋ”ን እንጂ “ጋር”ን አይደለም፡፡ ሃሳቡ ተያያዥነት ያለውን ወይም አብሮ የሚሄድን ሌላ ጉዳይ ማንሳት ከሆነ ደሞ መጠቀም ያለበት “ጋር”ን ነው ለዚያውም “ከዚህ…ጋር”ን፡፡

“ጋ” እና “ጋር”ን ማምታታት ጉልህ የትርጉም ስህተት ያመጣል፡፡ አንድ እናት ለልጃቸው ስልክ ደውለው “የት ነሽ?” ሲሏት “ወንድሜ ጋ ነኝ” ብላ ብትመለስ “አሁን የምገኘው የወንድሜ ቤት ውስጥ ነው፣” አሊያም “ያረፍኩት ወንድሜ ዘንድ ነው” ማለቷ ነው፡፡ በአጭሩ “ወንድሜ ጋ” ብላ ከመለሰችም “ወደ ወንድሜ ዘንድ በመሄድ ላይ ነኝ” ማለቷ ሊሆን ይችላል፡፡ “ከወንድሜ ጋር ነኝ” ካለች ግን እናቷን በምታነጋግርበት ወቅት ወንድሟ ከአጠገቧ አለ ማለት ነው፡፡

ብዙ ወጣት የሬዲዮ ጋዜጠኞች በ”ጋ” እና “ጋር” መካከል የትርጉም ልዩነት መኖሩን የሚያውቁ አይመስለኝም፡፡ እንደ መሰላቸው ነው የሚጠቀሙባቸው፡፡ “…አርቲስት እገሌ ጋር በተደጋጋሚ ስልክ ደውለን አልተሳካልንም” ሲሉ ሰምተን ሊሆን ይችላል፡፡ ለማለት ያሰቡት “አርቲስት እገሌ ጋ” ነው እንጂ “አርቲስት እገሌ ጋር ” አይደለም፡፡ አርቲስት እገሌ ጋር ሆነን ደወልን ማለት ከአርቲስቱ ጋር አብረን ሆነን ደወልን ማለት ነው እንጂ ወደ አርቲስቱ ደወልን ማለት አይደለምና፡፡

በሁለቱ ቃላት ዙሪያ ያለው መደበላለቅ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እንደመጣ ታዝቤያለሁ። የሬዲዮ ጋዜጠኞች ቀደም ሲል እንዳልኩት በተለይም ወጣቶቹ ጋ ችግር አለ፡፡ ጋዜጠኞቹ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኤዲተሮቻቸው ጋር መነጋገር ያለባቸው ይመስለኛል፡፡ ኤዲተሮቻቸውም ቢሆኑ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጐች ጋ የሚደርሱ ዓረፍተ ነገሮች ሲበላሹ ዝም ባይሉ ጥሩ ነው፡፡ ከዚሁ ጋር አያይዤ ላንሳና በቅርቡ የታተመ አንድ የግጥም መጽሐፍ ላይ ገጣሚው የአንደኛውን ስንኝ መጨረሻ ቃል በስህተት “ጋር” አድርጐ አንብቤያለሁ፡፡ ለማለት የፈለገው “ጋ” ወይም ዘንድ ነበር፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ በመስክ ስራ ላይ ከኔ ጋር እየሰራ የሚገኝ አንድ ወጣት የሁለቱን ፊደሎች ጉዳይ ለአዲስ አድማስ አንባቢዎች ላቀርብ ነው ስለው ለምን እኔን ምሳሌ አታደርገኝም? ይሄውኮ ልዩነታቸው ሳይገባኝ አንድ ሳምንት አለፈኝ” አለኝ፡፡

ለጨዋታ ያህል ይህንን ያህል ካልኩ ይበቃል። ከየወዳጆቻችሁ ጋር ተነጋገሩበት፡፡ እኔም ስጽፍ ተሳስቼ ከሆነ ስህተቴ የቱ ጋ እንደሆነ ጠቁሙኝ። በነገራችን ላይ ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ ጋር ያደረገችው የእግር ኳስ ጨዋታ እንዴት ነበር? አስደሳች ነበር አይደል፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ጋ ችግር ያለ አልመሰለኝም፡፡ አንዳንድ ተጫዋቾች ጋ ግን አለ፡፡ ብልጠት ይጐድላቸዋል፡፡ ያንን ፈጣን ቅብብላቸውን ተጠቅመው የባላጋራ ቡድን የፍፁም ቅጣት ክልል ጋ መጠጋትና መውደቅ ሲገባቸው…በደህና ሰንብቱ!

የ“ጋ” እና የ“ጋር” ልዩነት!

በታላላቆቹ የፖለቲካ ፈላስፎች በእነ ሆብስና ሩሶ አስተምህሮ መሰረት ግለሰቡ/ህዝቡ ስልጣኑንና በጎ ፈቃዱን በስምምነት መንግስት

ለሚባለው አካል ማስገዛት አለበት/አለባቸው ይሉናል። መንግስት የህብረተሰቡን ደህንነትና ንብረቱን የመጠበቅ ግዴታ አለበት፤ እንደ ሆብስ አባባል። ለሩሶ ደግሞ የመንግስት ተቀዳሚ ተግባሩ የህብረተሰቡን መብትና ነጻነት የማስከበር ነው፤ ይህ ግዴታው ያመዝናል። ሁለቱም ፈላስፎች ግብ ያደረጉት የማህበረሰቡ አንድነት እና ሠላም እንዲህ ማድረግ ከተቻለ ሰላማዊ ማህበረሰብ ይገኛልና ነው። የፍላጎት/ጥቅም/interest/ እና የመብት/right/ ውል እየተባሉ ለሁለት ቡድን ተከፍለው ምሁራዊ ትንታኔ ይሰጥባቸዋል፤ የሁለቱ ፈላስፎች ማህበራዊ ውል። የኛ ማህበረሰብ የመንግስት አመሰራረቱ ጥንታዊ ስለሆነ መሰረቱን በመብት ላይ አሊያም በፍላጎት ላይ ያድርገው አጥርተን አልተረዳነውም። በእኔ ግምት ግን ሃይማኖታዊና መንፈሳዊያን ስለሆንን አንዳች መለኮታዊ መንበር ላይ የተመሰረትን ይመስለኛል።

ይሄ ፍልስፍና የሚባል እራሱን የቻለ ወንበር ዘርግቶ አልተፈላሰፈም የምንለው ህዝባችን፤ ፍልስፍናን ለማህበራዊ፣ለመንግስታዊ እና ሃይማኖታዊ ህይወቱ እንደ ማጣፈጫ ቅመም እየመጠነ በያቅጣጫው ተክሏታል። በማህበራዊ ዘርፉ የስነምግባር መመሪያዎቻችን፣ የጎሳ/አካባቢ ሽምግልና፣ የመንደር ትምህርት ቤቶቻችን እና

ትንሹ መንግስትሌሎችም መዋቅሮቻችን የፍልስፍና ወዝ ያረፈባቸው ናቸው። በመንግስታዊ መዋቅሮች ውስጥ ነገስታት ፍትሃዊነትን፣የሞራል እና ፈጣሪን የመፍራት እሴቶችን ተላብሰዋል፡፡ በተጨማሪም ነገስታት እራሳቸውን የመግዛት ጥበብን በፍልስፍና ቅባት አብሰው ሽማግሎቻቸው አስተምረዋቸዋል። በሃይማኖታዊ ሥርዓታችን ምንም የማያከራክሩ የፍልስፍና መሰረታዊያንን እናገኛለን።

ማህበረሰባችን ጥንታዊ እንደ መሆኑና እንደ አጥቢያ ኮከብ ሥልጣኔውን ብልጭ አድርጎ እንደ መሰወሩ አንዳች የደበቀው ያልተገለጠልን መንግስት ያለው ይመስለኛል። ርዕሰ ጉዳዩ የሚያምታታ እንዳይሆን ግልጽ ለማድረግ ያህል፣ መንግስት እያልን የምናውቀውን/የሰየምነውን አካል መደበኛ መንግስት እንበለውና፤ ምናልባት ደግሞ በትላልቅ ተቋማት እራሱን ያልገለጸ፣ እንደ የለምለም መስክ ምንጭ ድምጽ ሳያሰማ ኩልል እያለ የሚፈስ፣ ስር ለስር የሚሰራ መንግስት ይኖር እንደሆን ደግሞ ትንሹ መንግስት እንበለው። ትንሹ መንግስት ባህል፣ ወግ፣ ልማድ፣ ሽምግልና፣ ጎሳ መሪ፣ ዕድር፣ እቁብ፣ ሰንበቴ፣ የቡና አጣጭ/ማህበር ወዘተ መገለጫው ሊሆን ይችላል።

የኛ የኢትዮጵያዊያንን ማህበራዊ መዋቅራት በመፈተሽ ምናልባት አንዳች የጋራ ጥቅም ተቋዳሽ ለማድረግ በማሰብ ይጠቅሙኛል የምላቸውን ሙግቶች (ምንም እንኳን በስርዓቱ ባላደራጃቸውም) ለመሰንዘር እሞክራለሁ። በዚያውም የፈረንጆችን የመንግስት መዋቅር በሃገራችን ሲተገበር የፈጠራቸውን ክፍተቶች መነቅነቅና መፈተሽ እፈልጋለሁ። በምርጫ 97 ወቅት በምስራቅ ጎጃም አካባቢ የተከሰተ ታሪክ ሁሌም ይመስጠኛል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ ባንድ ገበሬ ማህበር የቅንጅት ተወካዮች ለምርጫ ቅስቀሳ ገበሬውን ፖለቲካ ያጠጡታል፤ ስሜት የሚኮረኩሩና የፖለቲካ መንፈስን የሚያጦዙ ንግግሮች ሲካሄዱ ቆዩና፣ ባላገሮቹ አስተያየትና

ጥያቄዎችን መሰንዘር ይጀምራሉ። ከመሃልም አንድ ተሳታፊ “የምን ኮሮጆ፣ የምን ምርጫ ካርድ ነው የምታወሩት? በቃ እዚሁ ለምን አይለይልንም፤ ቅንጅት ነኝ የምትሉ በቀኝ፣ ኢህአዴግ ነኝ የምትሉ በግራ ተሰለፉ” አለ አሉ። መምረጥ መመረጥ በኛ ባህልና በፈረንጆቹ የፖለቲካ ባህል እንዲህ ነው ልዩነቱ የምርጫ ቀን፣ የምርጫ ካርድ፣ ምስጢራዊ ክፍል፣ የምርጫ ምልክት ይሏቸው ነገሮች ለኛ ሚዛን የሚደፉ አይመስሉም።

በጦርነትና በውስጣዊ ግጭት ምክንያት መደበኛው መንግስት ሲዳከም የማህበረሰቡን አንድነት አስጠብቆ የሚሄደው በትንሹ መንግስት ጥንካሬ ነው፤ መደበኛው መንግስት ጠንከር ሲል ደግሞ የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት ተቋቁሞ ቋንቋ ሳይገድበው አብሮ እየሰራ መኖር የቻለ ህዝብ። ምናልባትም በጣም ውስብስብና ከባድ ከሆኑት የዓለማችን ማህበረሰቦች ውስጥ አንዱ የኛ ማህበረሰብ ይመስለኛል። እርስ በርሱ እንደ ስውር ስፌት የማይታይና ሲታይም ደግሞ እንደ ሸረሪት ድር የሳሳ የሚመስል ያስተሳሰረው ማህበራዊ ክር አለ። የሶሲዮሎጂና አንትሮፖሎጂ ጥናቶችን በተጨማሪ መዳሰስ የሚያስፈልግ ይመስለኛል። አሁን ባነሳሁት ርዕሰ ጉዳይ ላይ ግን በኔ ግምት የኛን ማህበረሰብ ትንሹ መንግስት ያለው መሆኑን ማሳያ የሚሆኑ አራት ማህበራዊ እሴቶችን ልጠቀም፦

ሀ)ማህበራዊ ጤናማነት፦ የሽምግልና፣ የእርቅ፣ የምክክር፣ የአካባቢ ደህንነት/ቅራት ወዘተ… ጉዳዮችን ማህበረሰባችን የሚፈታባቸው/የሚያስተናግድባቸው መንገዶችን በቅርበት ብናጠናቸው ማህበራዊ ጤናማነትን ይወክልልናል። ይህ እሴታችን የፖለቲካ ሰዎቻችን (ተቃዋሚውም መንግስትም) የስልጣን ሽኩቻ ሲኖርባቸውና ወደ ጉልበት አንባጓሮ ቢያመራ ጣልቃ በመግባት የማረጋጋልት አቅም አለው።

ለ)ምጣኔ ሃብት፦እቁብ ፣ብድር፣ መዋጮ እና ሌሎች ቤሳ ቤስቲ ሲያጥረን ጎደሏችንን ለመሙላት የምንጠቀምባቸው የባህል ባንኮቻችንን ያጠቃልላል። ትዳር እንዳይፈርስ፣ ቤተሰብ እንዳይናጋ ማህበረሰብ እንዲረጋጋ፣ የራሳቸው ቁልፍ አስተዋጽዖ አላቸው፤ እነዚህ የገንዘብ ተቋማት።

ሐ)ማህበራዊ ፍቅር፦ የጡት አባት፣ ሞግዚት፣ አበልጅ፣ የተረት አባት፣ የሩቅ ዘመድ የቅርብ ጎረቤት የምንባባልባቸው ጎረቤቶቻችን። ከልጅ ልጅ ቢለዩ አመትም አይቆዩ የምንባባልበት መንደራችን። “እንዴ ይሄ ልጅ የእከሌት ልጅ አይደለም እንዴ? ከመቼው እንዲህ ተመዘዘ?” እየተባባልን ጉንጭና ግንባር እየሳምን የምናሰርጸው ማህበራዊ ፍቅር። በግድ አጣብቆ አንድ የሚያደርግ ማህበራዊ ሲሚንቶ ይመስለኛል።

መ)አመራር፦ አባወራዎች/እማወራዎች በየቤታቸው መታፈሪያ የሚሆኑ፤ የተከበሩ ሞገስ ያላቸው፣ ባለትህትና፣ በሞራል የበላይነት ቤተሰቦቻቸውን ቀጥ አድርገው የሚያስተዳድሩ አሉን። እነዚህም በየመንደራችን ብንቆጥራቸው ብዙ ይሆናሉ፤ ከነሱም ደግሞ ደረጃ ደረጃ አላቸው። የክብር የማእረግ ልዩነት። አንተም ተው አንቺም ተይ ማለትና ተጽእኖ ማድረግ የሚችሉ ብዙዎች አሉን። በይሉኝታም የምንታዘዛቸው። እነዚህ ሁሉ የየአካባቢዎቻችን ገዥዎች ናቸው። አስተዳዳሪዎቻችን።

የበጎ ፈቃዱን አብሮ ለመኖር ለባህሉ ያስገዛ ህዝብ ማለት ይሄነው። የሩሶን የሶሻል ኮንትራት ሃልዮትን ለትልቁ መንግስት ሳይሆን ለትንሹ መንግስት እንስጠውና ጉዳዩን ማህበረሰባችን ውስጥ ልክ እንደዚህ ፈትፍተን ስናየው፤ ለራሱ ባህላዊ ተቋማት እራሱን/የበጎ ፈቃዱን/ አስገዝቶ የሚኖር ህዝብ ስለ ሆነ፣ የራሱ ትንሽ መንግስት እንዳለው ፍንትው ብሎ ይታየናል። ማንም የማንም ባሪያ ሳይሆን፤ ማህበራዊ አንድነቱም ሳይዳከም እራሱን አዋቅሮ መተዳደሪያ ባህላዊ ህጎችን የሰራ ማህበረሰብ። ምልዓተ በጎ ፈቃድ የተላበሰ ነውና ትንሹ መንግስት ብንለው የሚያንስበት አይመስለኝም። ሁሉም በበጎ ፈቃድ እራሱን ለማህበራዊ አንድነቱ በባህልና ልማድ እራሱን ሲያስገዛ እያየነው ነውና።

በሩሶ የመንግስት/social contract/ አስተምህሮ ውስጥ ገዥዎች ብዙ ግዜ የራሳቸውን ጥቅም

Page 11: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

ገፅ 11 አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም

ተስፋዬ ድረሴ

ህብረተሰብ

ማስታወቂያ

ስደት ወደ ገፅ 21 ዞሯል

ለበርካታ ወገኖቻችን ወደ አረብ አገሮች መሰደድ ዋናዎቹ ምክንያቶች ደላሎች አይደሉም። እውነቱ ይፈንዳ፤ የችግሩ ምንጮች ወላጆች

ናቸው፡፡ ልጆቻቸው በጥሬ ፣በጥብስ፣በቅቅል መልክ ቢቀርቡላቸው እጃቸውን ታጥበው ለመብላት የማያቅማሙ “ሆዳም” ወላጆች! ይህ ሚስጥር ተፍረጥርጦ ካልወጣ በስተቀር ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች በስደት ማለቃቸው የሚቆም አይመስለኝም፡፡

ስሜቴን ወረቀት ላይ ለማስፈር ከአልጋዬ ላይ ከመነሳቴ በፊት ስደት ነክ ሰቆቃን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ላይ ሲደረግ የሰማሁት አሳሳች ትንተና አሳዝኖኝ፣ ብርድልብሴን ተሸፋፍኜ ለመተኛት ሞክሬ ነበር፡፡ ግን እንዴት ብዬ! ውስጤ ተቃጠለ፣ተቀጣጠለ፡፡

ለምን ነደድክ? በሉኝ፡፡ ከዛሬ አራት አምስት አመት በፊት ጀምሮ የስደት ችግር የሚሳበበው፣የሚላከከው በደላሎች ላይ ነው፡፡ ደላሎች ግን (ህገወጦችን ነው ያልኩት) ቢበዛ የሌባ ተቀባይ እንጂ ዋናዎቹ ሌቦች አይደሉም፡፡ የጥቆማ ስህተት ያለበት የወንጀል ምርመራን ይመስላል አካሄዱ፡፡ ወላጆች ደላሎችን ያማርራሉ፤ የችግሩ ሰለባ የሆኑት ዜጎችም እንዲሁ። የማህበራዊ ጉዳይ ባለሙያዎች፣ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ መስሪያቤቶች፣የመንግስት ባለስልጣናት፣የኪነጥበብ

ለወጣቶች ስደት ተጠያቂዎቹ ወላጆች ናቸው!

ባለሙያዎች ወዘተ… ወላጆች ከዚህ አስከፊ ችግር በስተጀርባ ደፈጣ ይዘው መቀመጣቸውን አይደፍሩም፡፡ ይሄ እያሳዘነኝ መሰለኝ የምነደው፡፡

አንድ አስቀያሚ ታሪክ ልንገራችሁና የተነሳሁበትን ነጥብ ላብራራ፡፡ ቦታው እንትን ክልል፣እንትን ዞን፣እንትን ወረዳ፣እንትን ቀበሌ፣እንትን መንደር ነው፡፡ ማንም እራሱን ለመከላከል እንዳይሞክር ብዬ ነው ስም ሳልጠቅስ የማወራላችሁ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡ ከአንድ አመት በፊት ጎረቤታም ወላጆች የሚከፈለውን ገንዘብ ከፍለው ልጆቻቸውን ወደ አረብ አገር ይልካሉ፡፡ ልጆቻቸው ላይ ኢንቨስት አደረጉ፣ ወይም ደሞ ልጆቻቸውን ለባርነት አሳልፈው ሰጡ ብለን ለማሰብ እንችላለን፡፡ አንደኛዋ ልጅ ብዙ ሳትቆይ አትራፊ ሆነችና ለወላጆችዋ ጠቀም ያለ ገንዘብ ላከች፡፡ በዚያ ገንዘብ ወላጆቿ ቤታቸውን አሳመሩ፤ ጥሩ ጥሩ ለባበሱ፤ አልፈው ተርፈው ጠመንጃ ገዙ፣ ወደ አደባባይም ኮራ ብለው መውጣት ጀመሩ (እነዚህ ወላጆች ጥገኞች ! በልጅ ላብ ያለፈላቸው ሰነፎች! መሆናቸውን የሚያውቅ ያውቃል)፡፡ ጓደኛዋ ግን አክሳሪ ሆነች፤ ልጃቸው ምንም ገንዘብ ስላልላከችላቸው እፍረት (የበታችነት) የተሰማቸው ወላጆች (ወይ በልጅ መወዳደር!) “ምነው ልጄ ጨከንሽ? አዋረድሽን? አብራሽ የሄደችው እኩያሽ ወላጆችዋን ስታኮራ አንቺ ምን ሆነሽ ነው ድምጥሽን ያጠፋሽው?” ብለው መልዕክት ይልኩላታል (እስቲ አስቡት… ይሄ ነገር ፈጣጣነት ፣ይሉኝታ-ቢስነት አይደለም ትላላችሁ?) ልጃቸው በምላሹ የጠና ችግር ላይ መሆንዋን ትነግራቸዋለች፡፡ እየደረሰባት ያለውን የጥቃት አይነት ተንትናም ችግሯ በቀላሉ እንደማይፈታ ታረዳቸዋለች፡፡ “ሆዳምና”

ይሉኝታ ቢስ ወላጆችዋ ግን የልጃቸውን ችግር ከምንም ሳይቆጥሩ “የፈለገው ችግር የኖረስ እንደሆን ከጓደኛሽ በምን ታንሺያለሽ”? ብለው ቁጣ አዘል መልዕክት ይልኩላታል፡፡ ያቺ መከረኛ ልጅ አሁንም መልስ መስጠት ነበረባት፡፡ “የምትሏት ልጅኮ ገንዘብ የምታገኘው ዝሙት አዳሪ ሆና ነው” በማለት ሳትወድ የግዷን የጓደኛዋን ሚስጥር ገልፃ ትነግራቸዋለች። ለልጃቸው ሳይሆን ለራሳቸው ክብርና ዝና ያሰፈሰፉት ወላጆች፤ “አንቺስ እንደሷ ሴት አይደለሽ? እሷ ያላት ነገር አንቺም አለሽ አይደለም እንዴ ታዲያ! ለምን እንደሷ አትሆኝም” ብለው ምላሽ ላኩላት፡፡ ይሄን ምን እንደምትሉት አላውቅም፡፡ እነዚህ ሰዎች ልጃቸው እጅና እግሯን ቆርጣ እየሸጠችም ቢሆን ገንዘብ ብትልክላቸው አይናቸውን በጨው አጥበው መቀበላቸው አይቀርም፡፡ ከዚያስ? ከዚያ ፀአዳ ነጠላና ጋቢ ለብሰው አደባባይ ይወጣሉ፡፡ ልጅት ሞተች ቢባልም አይከስሩም፤ ተቀምጠው (እድር ካላቸው) የእድር ብር ይበላሉ፡፡

አንባቢያን ሆይ፤ አሁን እየተናደድኩ ነው። የምናደደውም ልጆቻቸውን “እየተመገቡ”፣ ልጆቻቸውን እየለበሱ፣ ልጆቻቸውን ቤት፣ ልጆቻቸውን ጠመንጃ አድርገው ለመኖር በሚፈልጉ ሰነፍ፣ጥገኛ እና ሆዳም ወላጆች ነው፡፡ ለክፋቱ ደግሞ ብዛታቸው በመቶዎች ሳይሆን በብዙ ሺህዎች የሚቆጠር ነው፡፡ እንደታዘብኩት ከተሰዳጆች ብዛት የተነሳ ከሽማግሌና አሮጊት ወይም ትናንሽ ህፃናት በስተቀር ከቁጥር የሚገቡ ወጣቶች የሌለባቸው ወይም አልፎ አልፎ ብቻ የሚታይባቸው ወረዳዎች (መንደሮች) እየተፈጠሩ ነው፡፡ እዚህ ላይ አስተውሉ፤ ወጣቶች ከሌሎች መንደሮች ይሞታሉ።

እስቲ አሁን ደግሞ ፊታችንን ወደ ስደት ሰለባዎቹ እናዙር፡፡ የስደት ሰቆቃ ሰለባ የሆኑ ህፃናትና ወጣቶች ለስደት ምን እንዳነሳሳቸው ሲጠየቁ፤ የአብዛኞቹ መልስ “ወላጆቼን ለመርዳት፣ቤተሰቤን ለመደገፍ” የሚል ነው፡፡ እነዚህ ዜጎች በአንደኛ ደረጃ የሚኖሩት ለራሳቸው ሳይሆን ለወላጆቻቸው ነው ማለት ነው፡፡ አያሳዝንም? ይህ የሚያሳየን የተሰዳጆቹ ወላጆች ራሳቸውን ያልቻሉ ደካሞችና ድሆች መሆናቸውን ነው፡፡

ለመሆኑ ወላጆቻቸው ለምን ድሆች ሆኑ? ለወላጆች ድህነት ወይም ለድህነታቸው መባባስ አንደኛው ምናልባትም ዋነኛው ምክንያት ከአቅማቸው በላይ (ብዙ) ልጆችን መውለዳቸው ነው፡፡ እዚህ ጋ የድህነትን አዙሪት ተመልከቱልኝማ። ድሃ ወላጆች ድሃ (በኑሮ የሚጎሳቆሉ) ልጆችን ይወልዳሉ፡፡ የወላጆቻቸውን ድህነት በቅርበት እያዩ የሚያድጉ ልጆች ለወላጆቻቸው ያዝናሉ፤የባለ እዳነት ስሜትም ይሰማቸዋል፡፡ እናም ገና ራሳቸውን ሳይችሉ ወላጆቻቸውን ከድህነት ለማውጣት ሲሉ ከትምህርት ገበታ ርቀው ጊዜያዊ የገንዘብ ምንጭ መፈለግ ይጀምራሉ፡፡ ልጆቹ ወላጆቻቸውን ለመርዳት በሚያደርጉት ሂደት ተመልሰው ድህነት ውስጥ ሊዘፈቁ ይችላሉ፡፡

አንዳንዴማ እንዲህም ሊሆን ይችላል፡፡ ልጆች በረሃ ለበረሀ እየተሰደዱ፣ በባርነት ውስጥ ሆነው ለወላጆቻቸው ገንዘብ ይልካሉ፡፡ የልጅ ስፖንሰር ያገኙት ወላጆች ተጣጥረው ከችግር ለመውጣት በመፍጨርጨር ፈንታ ተጨማሪ ልጆችን ይወልዳሉ፡፡ አለመማር በሚያመጣው የአስተሳሰብ

Page 12: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 12 ህብረተሰብ

መኖሪያ ወደ ገፅ 21 ዞሯልማስታወቂያማስታወቂያ

Post Title: Auto Mechanic When applying please quote the post title and vacancy notice number EV11 Location: Legadembi Site Employment Type: Full time Salary: As per Company Salary Scale Application Deadline: 27 October 2013

Auto Mechanic Job Duties: The incumbent is expected to analyze malfunctions diagnose defects and repair, rebuild, and maintain mining machineries and components in the workshop as well as in the field. Maintains responsibility for workshop tools and equipments entrusted to him/her. Ability to basic job planning, to remove and install and major components, diagnose and repair all machine systems and components systematically, disassemble, rebuild and assemble all major components, fully read and understand parts, service manuals and programs such as SIS and ET, complete service reports, Spare parts lists and work orders correctly is a must. The incumbent is expected to be conversant with job steps, why they are conducted, any associated risk, and how to implement appropriated controls.

Job Requirements • Vocational diploma in Auto Mechanic or related fields • Minimum of two years work experience

Skills/Qualifications: The incumbent needs to have the necessary training or the work experience to complete the above listed duties to the specific machine suppliers standard following the correct procedures as outlined in the service manual and MIDROC gold’s policies and procedures manual for equipment maintenance for heavy duty maintenance.

Please send your application by e-mail to [email protected] or send your application & CV to MIDROC Gold Mine Plc. Human

Resource Services, P.O.Box 2318, Addis Ababa Only shortlisted candidates will be contacted.

Post Title: Auto Electrician When applying please quote the post title and vacancy notice number EV10 Location: Legadembi Site Employment Type: Full time Salary: As per Company Salary Scale Application Deadline: 27 October 2013

Auto Electrician Job Duties: Under close supervision of the Supervisor Electrical Services he/she analyzes malfunctions, diagnose defects and repair, rebuild, and maintain mining machineries and components in the workshop. Maintains responsibility for workshop tools and equipments entrusted to him/her. Ability to basic job planning, identify electrical components and identifying and effectively using tooling, diagnose, test and repair electrical systems, disassemble, inspect and assemble electrical components, read and understand parts and service manuals, complete service reports and work orders correctly is a must. The incumbent is expected to be conversant with job steps, why they are conducted, any associated risk, and how to implement appropriate controls.

Job Requirements • Vocational diploma in Auto Electricity or related fields • Minimum of two years work experience

Skills/Qualifications: The incumbent needs to have the necessary training or the work experience to complete the above listed duties to the specific machine suppliers standard following the correct procedures as outlined in the service manual and MIDROC gold’s policies and procedures manual for equipment maintenance.

Please send your application by e-mail to [email protected] or send your application & CV to MIDROC Gold Mine Plc. Human

Resource Services, P.O.Box 2318, Addis Ababa Only shortlisted candidates will be contacted.

MIDROC GOLD Mine PLC MIDROC GOLD Mine PLC

ጊፍት ኩባንያ ስለተሰማራባቸው የስራ ዘርፎች ይንገሩኝ?

ድርጅታችን በአሁኑ ሰአት በአራት የተለያዩ የሥራ ዘርፎች ውስጥ ነው የሚሰራው፡፡ በትሬዲንግ፣ በኢንዱስትሪ፣ በኮንስትራክሽንና በሪል እስቴት ስራዎች ላይ ተሰማርቷል፡፡ ጊፍት ትሬዲንግ ከተቋቋመ ሀያ ሁለት አመቱ ነው፡፡ የድርጅቶቹ እናት ኩባንያ ነው፡፡ በቅርቡ ለህንፃዎች ግብዓት የሚሆኑ እቃዎች ማምረቻ ፋብሪካ ከፍተን ሥራ ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነን፡፡ እስካሁን 1500 ለሚሆኑ ሰራተኞች የስራ ዕድል ፈጥረናል፡፡ ፋብሪካው ስራ ሲጀምር ደግሞ ቁጥራቸው ይጨምራል፡፡

ጊፍት ሪል እስቴት በቅርቡ ለሰራተኞቹ መኖሪያ ቤቶችን ሸልሟል፡፡ እስቲ ስለሽልማቱና አሸላለሙ ይንገሩን….

አንድ ድርጅት ስራውን ለማከናወን ካፒታልና የሰው ሀይል ያስፈልገዋል፡፡ በስራው ስኬታማ ሊሆን የሚችለው ሰራተኞች ተበረታተውና ጠንክረው ሲሰሩ ብቻ ነው፡፡ በድርጅታችን ውስጥ ለሶስትና አራት አመት የሰሩ ስምንት ጠንካራ ሰራተኞችን በስራ ብቃታቸው አወዳድረን ነው ቤት

ለሰራተኞቹ መኖሪያ ቤት የሸለመው ጊፍት ሪል እስቴት

ጊፍት ሪል እስቴት፤ የዛሬ ሁለት ሳምንት በስራቸው የላቀ ስኬት ላስመዘገቡ ስምንት ሠራተኞቹ መኖሪያ ቤት ሸልሟል፡፡ የመኖሪያ ቤቶች ሽልማት ሲሰጥ የመጀመርያው እንደሆነ የተናገሩት የድርጅቱ ባለቤት አቶ ገብረኢየሱስ ኢጋታ፤ ከዚህ ቀደም በስራቸው ውጤት ላስመዘገቡ ሠራተኞቻቸው ነፃ የትምህርት ዕድል መስጠታቸውን ገልፀዋል፡፡

ጋዜጠኛ ማህሌት ፋሲል ስለ ድርጅቱ አጠቃላይ እንቅስቃሴ፣ ስለመኖሪያ ቤት ሽልማቱና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ከጊፍት ሪል እስቴት ኩባንያ ባለቤት አቶ ገብረኢየሱስ ጋር አጭር ቃለምልልስ አድርጋለች፡፡

የሸለምናቸው፡፡ የቤት ሽልማቱ ወደፊትም ቀጣይነት አለው፡፡ በየአመቱ በስራቸው የላቀ ስኬት ላስመዘገቡ ሠራተኞች የመኖርያ ቤት ሽልማቱ ይሰጣል፡፡

ሽልማቱ የተሰጠው ለሪል እስቴቱ ሰራተኞች ብቻ ነው ወይስ በእህት ኩባንያ ውስጥ ለሚሰሩትም ነው?

አብዛኛዎቹ ተሸላሚዎች የሪል እስቴቱ ሰራተኞች ናቸው፡፡ በእህት ኩባንያ ያሉ ጥቂት ሰራተኞችም ተሰጥቷቸዋል፡፡ ወደፊት ግን ከአራቱም ድርጅቶች አወዳድረን ነው የምንሸልመው፡፡

ድርጅቱ ከዚህ በፊት ለሰራተኞች የቤት ሽልማት ሰጥቶ ያውቃል? ሰራተኞቹ የተሸለሙት መኖሪያ ቤት ምን ዓይነት ነው?

አፓርትመንት ነው፡፡ ከዚህ በፊት የቤት ሽልማት ሰጥተን አናውቅም፡፡ ነገር ግን በስራቸው የተለየ ብቃት ላሳዩ በርካታ ሰራተኞች የትምህርት እድል ሰጥተናል፡፡ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ አስተምረናል፡፡ አሁንም እያስተማርናቸው ያሉ ሰራተኞችም አሉ፡፡ የትምህርቱን ሙሉ ወጪ የሚሸፍነው ድርጅቱ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት አራት ሰራተኞችን በማስተርስ ድግሪ እያስተማርን

ሲሆን ለአንድ ተማሪ ሁለት መቶ ሺህ ብር ገደማ ነው የምንከፍለው፡፡ የሚማሩትም ውጪ አገር ነው። አንድ ሰራተኛ ሲማር ራሱን ብቻ አይደለም የሚጠቅመው፡፡ ድርጅቱንም ይጠቅማል፡፡

የቤት ሽልማት የሰጣችሁት በየትኛው የስራ ዘርፍ ላሉ ሰራተኞች ነው?

ሽልማቱን የሰጠነው በኢንጂነሪንግና በማኔጅመንት ውስጥ ላሉ ሰራተኞች ነው፡፡ ለኢንጂነሮች ከሶስት አመት በላይ በድርጅታችን ተግተው ለሰሩ፣ በማኔጅመንት ደግሞ ከአራት አመት በላይ ላገለገሉ ታታሪና ትጉህ ሰራተኞች

አወዳድረን ነው የሸለምነው፡፡የቤቶቹ ዋጋ ምን ያህል ነው? ለሰራተኞች የሰጠነው በሶስት ደረጃ ነው፡፡ ባለ

ሶስት መኝታ ክፍል በአንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ ብር፣ ባለ ሁለት መኝታ ቤቱ ዘጠኝ መቶ ሀያ ዘጠኝ ሺህ ብር፣ ባለ አንድ መኝታ ቤት ስድስት መቶ አስር ሺህ ብር ነው የሚያወጡት፡፡

ለደንበኞች በቅርቡ የምታስረክቧቸው ቤቶች ይኖራሉ?

በህዳር ወር በሳይት አንድና ሁለት ላይ የሚገኙ ከሀምሳ በላይ ቤቶችን ለማስረከብ ዝግጅት ጨርሰናል፡፡ ቪላና ታውን ሀውስ የሚባሉ ቤቶች ናቸው፡፡ መጋቢት ላይም እንዲሁ የአፓርትመንት ቤቶች የማስረከብ እቅድ አለን፡፡

በክልሎችስ መኖሪያ ቤቶች ትገነባላችሁ?እስካሁን አልጀመርንም፤ ምክንያቱም የያዝነውን

ስራ ማጠናቀቅ አለብን፡፡ ሪል እስቴት ጥንቃቄ ይፈልጋል፤ በእቅዳችን ውስጥ ግን ተይዟል፡፡ በክልሎችም የመስራት ሃሳብ አለን፡፡ ይሄ የማይቀር ነው፡፡

አንዳንድ የሪል እስቴት ኩባንያዎች ለደንበኞች የገቡትን ቃል ባለመፈፀማቸው የተፈጠረው ጥርጣሬ ስራችሁ ላይ ተፅዕኖ አልፈጠረም? እንዲህ ያሉ ችግሮች የሚከሰቱት በምን ምክንያት ነው?

እስካሁን ምንም ችግር አልፈጠረም፤ ምክንያቱም ቤቶቹን ቶሎ ሰርተን እናስረክባለን። የችግሮቹ መንስኤ እንደሚመስለኝ ሁለት ናቸው። ውስጣዊ ችግርና ውጫዊ ችግር የምንለው ነው። በደንብ ሳይቀናጁ ስራ ይጀምሩና አይሳካም ሁለተኛው ደግሞ የብዙ ሪል እስቴት ችግር የሆነው ውጫዊ ችግር ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ የመጀመሪያው የኮንስትራክሽን

Page 13: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 13 ማስታወቂያ

Page 14: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 14 ዋናው ጤና

መንግሥቱ አበበ

ህይወት ወደ ገፅ 25 ዞሯል

አንድ ልጅ ተፀንሶ እስኪወለድ ድረስ ያለው የሰው ልጅ ዕድገት ፍጥነት በጣም አስገራሚና የሚደንቅ ነው፡፡ በአንደኛው ወር ብቻ በጣም ኢምንቷ ኦርጋኒዝም

(አንዱ ከሌላኛው አካል ጋር የሚደጋገፉ ጥቃቅን ኅዋሳት) በተፀነሰበት ወቅት ከነበረው ክብደት 10ሺህ ያህል ጊዜ ይጨምራል፡፡ በመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት፣ ከኢምንት ውሃማ ነገር፣ ቁጥር ስፍር ወደሌለው ውስብስብና ጅምር የሰው ቅርፅ ይለወጣል፡፡ ቅርፁ ባይጠናቀቅም ልጅ እንደሚሆን ግን መገንዘብ ይቻላል፡፡

እያንዳንዱ ሂደት ይሆናል ብሎ ለማመን የሚከብድና ግምትን የሚፈታተን ረቂቅ የዕድገት ለውጥ ነው፡፡ አንደኛው የለውጥ ሂደት ለሚቀጥለውና ለዋነኛው ሁለንተናዊ ዕቅድ፣ በሚያስገርም ፍፁም ትክክለኛነት ያስተላለፋል። ይህ 267 ያህል የሚፈጀው የትራንስፎርሜሽን ወይም የለውጥ ሂደት፣ የራስና የማንኛውም ሰው የማይታመን የሕይወት ታሪክ የሚጀመርበት የዕድገት ሂደት ነው፡፡

ተቃራኒ ፆታ የሆኑ ሰዎች ወሲባዊ ግንኙነት በሚፈፅሙበት ጊዜ፣ ያኮረተ ወይም ለመፀነስ ዝግጁ የሆነ የሴቷ እንቁላል፣ ከወንዱ የዘር ፍሬ (ስፐርም) ጋር ሲገናኝ ወዲያውኑ ከመቀፅበት፣ የሴቷን ባህርያት የያዙ 23፣ የወንዱን ባህርይት የተሸከሙ 23፣ እንዲሁም ሁለት ፆታ ወሳኝ ከሆኑ ክሮሞዞሞች (የዝርያ ሐረግ) ጋር በመሆን 48 ክሮሞዞሞች፣ የተሟላ የዘር ሐረግ ባቀፈው ሴል (ኅዋስ) እምብርት ሆነው የመጀመሪያውን የኅዋስ ክፍፍል (ሴል ዲቪዥን) ለመጀመር በከፍተኛ ፍጥነት በመሽከርከር ይዋሃዳሉ፡፡

የእናቱንና የአባቱን የዘር ውርስ ይዞ የተፀነሰው እንቁላል መጠን በጣም የሚገርም ነው፡፡ በእንግሊዝኛው ፊደል አይ (i) አናት ያለችውን ነጥብ የሚያክል ነው፡፡ ነገር ግን ይቺ ኢምንት ፅንስ፣ ከሁሉም ልጆች ልዩ የሆነውን ልጅና ከማንኛውም ወላጅ ልዩ የሆኑትን የእናቱንና የአባቱን የወ/ሮና የአቶ እገሌን የዘር ሐረግ አጠቃላ ይዛለች፡፡

ኅዋሳቱ መከፋፈል ሲጀምሩ (አንዱ ሴል ሁለት፤ ሁለቱ አራት፤ አራቱ ስምንት፣ … እያለ ይቀጥላሉ) ፅንሱ በሴቷ ግራና ቀኝ ጐን በሚገኙት የእንቁላል መተላለፊያና የፅንስ መፈጠሪያ (ፋሎፒያን ቲዩብ) በአንዱ ውስጥ እየተንሳፈፈ ወደ ማኅፀን ጉዞ ይጀምራል፡፡ ከቲዩቡ እስከ ማኅፀን ያለው ርቀት 5 ሳ.ሜ ያህል (2 ኢንች) ቢሆንም፣ ፅንሱ ማኅፀን ለመድረስ ሦስት ወይም አራት ቀናት ይፈጅበታል፡፡ ብዙ ጊዜ ፅንሱ ማኅፀን የሚደርሰው በ16ኛው የኅዋስ ክፍፍል ደረጃ ነው፡፡

በእነዚህ የመጀመሪያ ቀናት እንኳ አስገራሚ ለውጥና ዕድገት ስለሚካሄድ ሁለት የተለያዩ ሴሎች በግልጽ ማየት ይቻላል፡፡ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚሹትንና የልጁን የውጪኛ አካላት የሚፈጥሩትን፣ ዝርግና በፍጥነት ጠላቂ ኅዋሳትና የልጁን የውስጠኛ አካላት የሚፈጥሩ ክብና የሚያምሩት በዝግታ ጠላቂ

ኅዋሶች ይፈጠራሉ፡፡ ከአራተኛው እስከ ስድስተኛው ወይም ሰባተኛ

ቀን ድረስ የፅንሱ መጠን ከነጥብ ከፍ ብሎ የስፒል (የወረቀት መርፌ) አናት ያህላል፡፡ በዚህ ጊዜ የኳስ (ኤግ ቦል) ቅርፅ የያዘው እንቁላል፣ በሙቅና በጥቁር ፈሳሽ በተሞላው ማኅፀን ውስጥ ይንሳፈፋል፡፡ ልስልሱ የማኅፀን ግድግዳ ከጥቃቅን የደም ስሮች ጋር ተጠላልፎ ይሰራል፡፡ ፅንሱ በዚህ ልስልስ ግድግዳና ስፖንጅ በመሰለ ነገር ላይ ይጣበቅና ራሱን በኃይል ይቀብራል፡፡ ከዚያም፣ በማቆጥቆጥ ላይ ካሉት ጥቃቅን ፀጉር መሰል ነገሮች (ካፒላሪስ) ጥቂቶቹን በመክፈት በውስጣቸው የያዙትን ደም ያስወጣል፡፡

ኳስ መሰሉ እንቁላል (ፅንስ) በመቶዎች የሚቆጠሩ በጣም ጥቃቅንና በፍጥነት አዳጊ ቪሊ (Villi) የተባሉ ፀጉር መሰል ነገሮች በመላ አካሉ ላይ ያበቅላል፡፡ ጥቃቅን ተክሎች ስራቸውን በጥልቀት ሰደው ምግብ እንደሚስቡት፣ ቪሊዎቹም፣ ስራቸውን እጅግ ጥቂት በሆነው ደም ውስጥ ተክለው ኦክስጂንና ምግብ ይመጣሉ፡፡ ምግቡም፣ ኳስ መሰሉን እንቁላል በፍጥነት ያሳድገዋል፡፡

እነዚህ ሁሉ ለውጦች ሲከናወኑ እናቲቱ ማርገዟን እንኳ አታውቅም፡፡ ምክንያቱም ቢያንስ ከ21ኛው ቀን በፊት ማርገዟን ማወቅ ስለማትችል ነው፡፡

በዚህ ጊዜ፣ ሞለል ያለው ማኅፀን ውስጥ የሚገኙት በርካታ ክብ ሴሎች፣ ራሳቸውን ወደ ትናንሽ አስኳልና አሚኒዮ (aminion) ከረጢትነት ይለውጣሉ፡፡ ከረጢቶቹ በሚነካኩበት (በሚገናኙበት) ስፍራ ደግሞ ሦስተኛ ከረጢት ይፈጥሩና ባለ ሦስት ደረጃ ሞላላ ንጣፍ ይፈጥራሉ። አሚንዮ ከረጢቱ ልጁ እስኪወለድ ድረስ በጣም ጠቃሚና አስፈላጊ ቢሆንም የአስኳል ከረጢቱ ግን ወደፊት ምንም ጥቅም የለውም፡፡ አሁን ራሱን ወደ ሽል እስኪለውጥ ድረስ ከፍተኛውን ሚና የሚጫወተው ቀለል ያለው ባለ ሦስት ደረጃ ኅዋስ (ሴል) ነው፡፡

እያንዳንዱ ንብርብር ንጣፍ ወደፊት ልጅ ለሚሆነው ሽል የተለያየ ኅዋስ መፍጠሪያ ይሆናል። አንደኛው ንጣፍ የነርቭ ሲስተም፣ ቆዳ፣ ፀጉር፣ የጣት ጥፍር፣ የጥርስ መስተዋት፣ የአፍንጫና የጉሮሮ ግድግዳ ሴሎች መፍጠሪያ ይሆናል፡፡ መካከለኛው ንጣፍ፤ የሽሉ ጡንቻ፣ አጥንትና ጅማት፣ ደምና የደም ስሮች፣ ኩላሊትና የድድ መፍጠሪያ ሴል ይሆናል። ሦስተኛው ንጣፍ ደግሞ አንጀትና ለአብዛኛው

መተንፈሻ አካላት ሲስተም መስሪያነት ይውላል፡፡ ቀጣዩ ለውጥ ወይም ትራንስፎርሜሽን ደግሞ፣

ምናልባት ከሁለም የላቀው ተአምራዊ ሂደት ነው፡፡ በ19ኛው ወይም በ20ኛው ቀን፣ ሞለል ያለው ክብር ነገር፣ በአካሉ ላይ በሁለቱም በኩል ወደታች የሚሄድ ጐድጐድ ያለ ቦይ መሳይ ነገር ይፈጠራል፡፡ ቦዮቹ በአንድ ጫፍ ይገናኛሉ፤ ያ የልጁ ራስ መሆኑ ነው። ቦዮቹ ከፍና ዝቅ እያሉ በመተጣጠፍ ሲቀራረቡ ሞላላው ክብ ነገር የግማሽ ጨረቃ ወይም የደጋን ቅርፅ ይይዛል፡፡ የደጋኑ የውጪኛ እጥፋት (Curve) የልጁ ጀርባ ይሆናል፡፡ በጥቂት ቀናት ውስጥ ደግሞ አከርካሪን የሚጠቁም ነገርና አዕምሮ ውስጥ የሚገኙ ነገሮች፣ በራስ መጨረሻ የሚገኘውን ጐድጐድ ያለ ስፍራ ሙላት ይጀምራሉ፡፡ ከዚያ በኋላ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ እጅና እግር መሆኑን የሚጠቁሙ ትናንሽ ቡጥ መሰል ነገሮች ማቆጥቆጥ ይጀምራሉ፡፡ በ21ኛው ቀን፣ በጣም አስፈላጊና ጠቃሚ የሆነው ልብ ይፈጠራል፡፡ ከዚያም ያ ልብ ከ10 ቀናት በኋላ መምታት ይጀምራል፡፡

ፅንሱን የያዘው ሞለል ያለ ከረጢት (እንግዴ ልጅ) ከእናቲቱ ጋር የሚገናኘው፣ በእትብት ነው፡፡ እትብቱ የተሠራው ደግሞ እንደክር ወይም ገመድ በተጠላለፉ ኅብረ-ሴል (Tissues) ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ የእትብቱ ርዝመት እስከ 56 ሳ.ሜ (22 ኢንች) ሊደርስ ይችላል፡፡ በፕሮቲን ፈሳሽ (aminotic sac) በተሞላው ሞለል ያለ ከረጢት (እንግዴ ልጅ) ውስጥ የግማሽ ጨረቃ ወይም የደጋን ቅርፅ ያለው በጣም ትንሽ ሽል በኅብረ-ሴል ከረጢት ሁለቴ ተጠቅልሎና በሌላ የኅብረ-ሴል ኳስ ውስጥ ሆኖ፣ እንደስፖንጅ በሚለሰልሰውና በሚመቸው የማኅፀን ግድግዳ ራሱን ይቀብራል፡፡ 98 በመቶ ንፁህ ውሃ በሆነ ፈሳሽ የተሞላው ከረጢት (እንግዴ ልጅ) ተግባር፣ የሽሉ መቀመጫ ቤት ብቻ ሳይሆን፣ ንቅናቄንም (Shock) በማርገብ ረገድ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡

ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ሽሉ በፍጥነት የልጅ ገጽታ እየያዘ ይሄዳል፡፡ በሁለተኛው ወር፣ ከራስ እስከ መቀመጫው (ቂጥ) ያለው ርዝመት 2ሳ.ሜ ተኩል (1 ኢንች) ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን አፍንጫ፣ አፍ፣ ጆሮና ዓይን ሊሆን እንደሚችል የሚጠቁም ጐድጐድ ያለ ነገር አለው፡፡ ከሦስተኛው ወር መጨረሻ ጀምሮ ሽሉ፣ ከ7ሳ.ሜ ተኩል በላይ (3 ኢንች) ሲረዝም፣ ክብደቱ ደግሞ ከ28 ግራም በላይ ይሆናል፡፡ የተለያዩ የአካል ሲስተሞቹም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ በግልፅ ያሳያሉ ወይም ይለያሉ።

በዚህ ጊዜ ዓይንና ሽፋሽፍቱ የተፈጠሩ ቢሆንም ዓይኑ ግን ለጊዜው እንደተከደነ ነው፡፡ ፆታም ይለያል፡፡ የእጅና የእግር መፈጠር ከመጠናቀቁም በላይ ሁለቱም ጣቶች ጥፍር አብቅለዋል፡፡ ሽሉ እጅ እግሩን ማንቀሳቀስ ቢጀምርም፣ እናቲቱ ግን ይህን የመጀመሪያ ጊዜ እንቅስቃሴ መገንዘብ አትችልም። ለሁለት ወራት ሲመታ የቆየው ልብ ጡንቻም ጠንክሯል፡፡

በዚህ ጊዜ ሽሉ መዋጥ ብቻ ሳይሆን መተንፈስን ለመለማመድ ይመስላል፣ ዙሪያውን ከከበበው የፕሮቲን ፈሳሽ ጥቂት ይጐነጫል፡፡ ፈሳሹ ወደ ሳንባው ሲገባ፣ ሽሉ የመተንፈሻ ጡንቻዎቹን በመጠቀም ያስወጣዋል፡፡ ይህ ሁሉ ልምምድ ሲሆን፣ ሽሉ እስኪወለድ ድረስ ኦክሲጅንና ምግቡን የሚያገኘው ከእናቱ ነው - በእትብት አማካኝነት። እነዚህ ሁሉ አስገራሚ ለውጦችና ዕድገቶች የሚከናወኑት በመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት ነው፡፡ አሁን የእናቲቱ ማኅፀን ማደግ ቢጀምርም ምናልባት በራሷ ዓይነ ካልሆነ በስተቀር የሆዷን ማደግ ሌሎች አይገነዘቡትም፡፡ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ሽሉ ወደ ልጅ መጠን የሚያድግ ሲሆን አዲስ ልጅ ሆኖ ሲወለድ የሚያደርገው ነገር ችሎታም ቀስ በቀስ ያድጋል፡፡

እናትና ሽሉ የሚገናኙት በእትብት ብቻ ነው። እትብቱ ነርቭ ስለሌለው፣ የእናትና የሽል ነርቭ

ሕይወት በማህፀን ዓለም

መታሰቢያ ካሣዬ

መታሰቢያ ካሣዬ

ህፃናት በተቅማጥ በሽታ ሲጠቁ በአፋጣኝ የሰውነታቸውን ፈሳሽ በመተካት ከሞት የሚታደጋቸውና አቅማቸው እንዲመለስ የሚያደርገው የኦ.አር.ኤስ እና ዚንክ ውህድ የሆነ “ለምለም ፕላስ” የተሰኘ አዲስ ምርት ገበያ ላይ ዋለ፡፡

በዲኬቲ ኢትዮጵያ ተዘጋጅቶ ለገበያ የቀረበው አዲስ ምርት፤ ህፃናት በተቅማጥ በሽታ በሚጠቁበት ጊዜ ከሰውነታቸው የሚወጣውን ፈሳሽ ከመተካትና አቅማቸውን ከመመለስ ባሻገር በተከታዮቹ ሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ በተቅማጥ በሽታ የመያዝ ዕድላቸውን የሚያስወግድና የሚከላከል መሆኑ ተጠቁሟል። ከዚህ በተጨማሪም ውህዱ ህፃናቱ በተቅማጥ በሽታ ቶሎ ቶሎ እንዳይያዙ የሚያደርግ አቅም እንደሚገነባላቸውም ተገልጿል፡፡

ምርቱ የተዘጋጀው ዲኬቲ ኢትዮጵያ በማይክሮ ኒውትሬት ኢንሺየቲቭ በኩል በአለማቀፍ የካናዳ መንግስት የልማት ትብብር በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ሲሆን በአገር ውስጥ እየተመረተ አገልግሎት ላይ እንደሚውልም ተገልጿል፡፡ ስርጭቱ የሚከናወነው በዲኬቲ ኢትዮጵያ ሲሆን በመንግስትና የግል ተቋማትና የመድሃኒት መሸጫ መደብሮች ውስጥ በማከፋፈል ለህብረተሰቡ እንዲዳረስ እንደሚደረግ ከትላንት በስቲያ በሂልተን ሆቴል በተካሄደ የምርት ማስተዋወቂያ ስነስርዓት ላይ ተገልጿል፡፡

ህፃናትን በተቅማጥ ከመሞት የሚታደግ አዲስ

ምርት ገበያ ላይ ዋለ

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲና ሄይንሪች ሄይን በተባለ ጀርመናዊ ዩኒቨርስቲ ትብብር በአሰላ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ የተሰራው የቆላ በሽታዎች ምርምር ማዕከል ባለፈው ረቡዕ ተመረቀ፡፡

Institute of Research for Tropical Infectious Disease የተባለው የምርምር ማዕከል፤ በጀርመን ዩኒቨርስቲ የገንዘብ ድጋፍ ተሰርቶና ሙሉ የመገልገያ ቁሳቁሶቹ ተሟልተውለት ለምረቃ በቅቷል፡፡

በአሰላ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ በተከናወነው የማዕከሉ የምረቃ ስነስርዓት ላይ

የቆላ በሽታዎች ምርምር ማዕከል ተመረቀበአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የአሰላ ጤና ሳይንሶች ትምህርት ቤት ዲን የሆኑት ዶ/ር ለገሰ ታደሰ እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ በጀርመናዊው ዩኒቨርስቲ የማቴሪያል፣ የፋይናንስና የቴክኖሎጂ ድጋፍ የሚንቀሳቀስና ዘመናዊ ሳይንሳዊ ምርምሮች የሚካሄዱበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የህክምና ሙያ በምርምር መታገዝ አለበት ያሉት ዶ/ር ለገሰ፤ ደረጃውን በጠበቁ የምርምር መሳሪያዎችና የላብራቶሪ ዕቃዎች የተሟላው ማዕከሉ፤ ዩኒቨርስቲው እየሰጠ ያለውን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርቶች ለማገዝና በህክምና ሙያ ብቃት ያላቸውን ባለሙያዎች ለማፍራት ያግዛል ብለዋል፡፡

በማዕከሉ በተለይም በቆላ በሽታዎችና (ካላዘር፣

የቆዳ በሽታና ወባ) በጉበት በሽታ ላይ ትኩረት ያደረገ ምርምር የሚካሄድ ሲሆን እንደኤችአይቪ ፣የሳንባ ነቀርሳና ሌሎች ተያያዥ በሽታዎችን በተመለከተም ምርመራና ጥናት እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡

የአሰላ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እ.ኤ.አ በ2009 ዓ.ም በአዳማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስር ተቋቁሞ በጤና ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎችን እየተቀበለ የሚያሰለጥን ሲሆን ከመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች መካከል 90 የሚሆኑትን በቅርቡ አስመርቋል። በአሁኑ ወቅት አንድ ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎችን መደበኛና መደበኛ ባልሆኑ ፕሮግራሞች ተቀብሎ በማሰልጠን ላይ የሚገኝ መሆኑም ተገልጿል፡፡

Page 15: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 15 ማ

ስታ

ወቂ

ስካይ ባስ ትራንስፖርት ሲስተም አክስዮን ማህበር የባለአክስዮኖች 5ኛ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ እሁድ፣ ህዳር 1 ቀን 2006 ዓ.ም. በኤግዚብሽን ማዕከል ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ጀምሮ ያካሂዳል፡፡

የጠቅላላ ጉባዔው አጀንዳ1.1 የጉባኤውን አጀንዳ ማፅደቅ1.2 የ2005 የበጀት ዓመት የዳይሬክተሮች ቦርድ ሪፖርት ማዳመጥ፣1.3 የ2005 የበጀት ዓመት የውጪ ኦዲተሮች ሪፖርት ማዳመጥ፣1.4 በቀረቡት ሁለት ሪፖርቶች ላይ ተወያይቶ ማፅደቅ፣1.5 የውጭ ኦዲተሮች ሹመት ማፅደቅና የክፍያ መጠን መወሰን፣1.6 በተጓደሉና የሥራ ዘመናቸውን በጨረሱ የቦርድ አባላት ምትክ መምረጥ፣1.7 የ2005 የበጀት ዓመት ትርፍ አከፋፈል ላይ መወሰን፣1.8 የጉባኤውን ቃለ ጉባኤ ማፅደቅ

ማሳሰቢያበጉባኤው ላይ በግንባር መገኘት የማትችሉ ባለአክስዮኖች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት አንስቶ እስከ ጥቅምት 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ ቄራ መላቅ ትሬዲንግ ሕንፃ ላይ በሚገኘው የኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት በመቅረብ ድርጅቱ ባዘጋጀው የውክልና ቅፅ ላይ በመሙላት ተወካዮቻችሁን ማሳተፍ የምትችሉ ሲሆን፤ የባለአክስዮኖች ሕጋዊ ተወካዮች አግባብነት ካለው የመንግስት አካል የተሰጠ የውክልና ስልጣን ሰነድ ይዛችሁ በመቅረብ በጉባኤው ላይ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

ጉባኤው ተወያይቶ የሚያስተላልፋቸው ውሳኔዎች በጉባኤው ባልተገኙ አባላት ላይ የፀና ይሆናል፡፡

የስካይ ባስ ትራንስፖርት ሲስተም አ.ማ.የዳይሬክተሮች ቦርድ

አድራሻ፡ ዋናው መስሪያ ቤት ቄራ መላቅ ትሬዲንግ ሕንፃ ላይ፣ ስልክ

ቁጥር 0114673331አዲስ አበባ

የስካይ ባስ ትራንስፖርት ሲስተም አ.ማ.

የባለአክስዮኖች 5ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔየስብሰባ ጥሪ

ማስታወቂያማስታወቂያ

We would like to invite all interested and qualified individuals for the following posts.

1. Position: High School TeacherQualification: BED Degree in Natural Science, Social Science or Language Studies from a recognized institution with very good command of English language.Experience: 2 years or above.

2. Position: Elementary TeacherQualification: BED, BA or BSC Degree in Natural Science, Social Science or Language Studies from a recognized institution with very good command of English language.

3. Position: Kindergarten TeacherQualification: Degree in any field of study from a recognized nstitution with very good command or English language.Gender: Female

4. Position: Copy typistQualification: Diploma or 10+3 in Information Technology or related field of study from a recognized institution.Gender: Female

5. Position: CashierQualification: Degree, Diploma or 10+3 Accounting or related field of study from recognized institution.Gender: Female

6. Position: SecretaryQualification: Degree or Diploma or 10+3 secretarial science and office management or related field of study from a recognized institution with very good command of English language.Gender: Female

For All positions experience: PreferableFor All positions salary: NegotiableAll interested applicants need to apply in person at School of Tomorrow, Lem branch which is located around Lem Hotel, Megenagna during working hours. Applicants need to submit their application letter, CV and copy of their credential starting from October 16,2013 until October 31,2013. If you have any question please do not hesitate to call us at 011-6 63 19 11 or 011-6 18 21 98.N.B All submitted documents are not returnable.

VACANCY ANNOUNCEMENTSCHOOL OF TOMORROW

ADDIS ABABA

The Cultural Section of the Embassy of the I.R. of Iran is pleased to announce that it holds a free course on Iranology (the general survey of Iran) and Persian Language.

Iranology course contains:1.Persian civilization, culture and history2.Basic concepts of diplomacy and Iran in the international arena. 3.Fundamentals of literature and Persian masterpieces4.Research Methodology5.Ethio-Iran relations since Axumite civilization and more

The course will be given once a week for three months. Persian Language course is given twice and it contains 1. Persian Alphabets 2. Persian Grammar 3. Conversion 4. Persian poemsCertificate will be issued only after successful completion of the course.

Applicants should bring their CV and a copy of relevant documents together with a passport size photograph until the 26th October 2013. Understanding English is Mandatory. Address: Bisrate Gabriel, around Dagem Millennium Hotel, in front of AU chairperson’s RESIDENCE, Iran Embassy No. 2

For more information, please contact: Tel: 011-3-72-75-52\53 P.O. Box: 70488

E-mail: [email protected]

Embassy of the Islamic Republic of Iran Cultural Section Addis Ababa

10th Round Free Iranology and Persian Language Courses Registration

ማስ

ታወ

ቂያ

ተ.ቁ የሥራ መደብ ተፈላጊ ችሎታ1 የምርት እና ቴክኒክ

ክፍል ኃላፊ• ዲግሪ በሞያው አራት ዓመትና ከዚያ በላይ ያገለገለ ሆኖ• በወረቀት ፋብሪካ የሠራ ወይንም በተመሳሳይ ሙያ ላይ የሠራ ቢሆን ይመረጣል፡፡

2 ሲኒየር ኤሌክትሪሺያን • ዲግሪ 2 ዓመት ዲፕሎማ 4 ዓመት • በወረቀት ፋብሪካ የሠራ ወይንም በተሳሳይ ሙያ ላይ የሠራ ቢሆን ይመረጣል

3 ቦይለር ኦፕሬተር • ሁለት አመትና ከዚያ በላይ የሠራ ሆኖ• በወረቀት ፋብሪካ የሠራ ወይንም በተመሳሳይ ሙያ ላይ የሠራ ቢሆን ይመረጣል፡፡

4 ማሺን ኦፕሬተር • በማሺኒስት የቴክኒክና ሙያ ት/ቤት ዲፕሎማ • 4 ዓመትና ከዚያ በላይ የሰራ/የሠራች• በወረቀት ፋብሪካ የሠራ ወይንም የሠራች

5 ሲኒየር ማሽኒስት • በማሺኒስት የቴክኒክና ሙያ ት/ቤት ዲፕሎማ• 4 ዓመትና ከዚያ በላይ የሰራ/የሠራች

6 ሲኒየር መካኒክ • በሜካኒክነት ወይም በጠቅላላ መካኒክ (በኢንዱስትሪያል መካኒክ) ዲፕሎማ • እና በአውቶሜካኒክ ዲፕሎማ ለሁለቱም የስራ መደቦች• በሙያው 4 ዓመትና ከዚያ በላይ የሠራ• በወረቀት ፋብሪካ የሠራ ወይንም በተመሳሳይ ሙያ ላይ የሠራ ቢሆን ይመረጣል፡፡

7 ሲኒየር አካውንታት • በአካውንታንት በ ቢኤ ዲግሪ የተመቀ/ች• በሙያው 4 ዓመትና ከዚያ በላይ የሰራ ሆኖ• የድርጅቱን ሒሣብ አስመርምሮ ማዘጋጀት የሚችል፡፡ • በኃላፊነት የሠራ ቢሆን ይመረጣል

8 ጠቅላላ አገልግሎት • በሰው ኃይል አስተዳደር ወይም በማኔጅመንት ዲፕሎማ ያለው• በሞያው አራት ዓመትና ከዚያ በላይ ያገለገለ• በወረቀት ፋብሪካ የሠራ ወይንም በተመሳሳይ ሙያ ላይ የሠራ ቢሆን ይመረጣል

9 ኬሚስት • በኬሚስት የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው • በክሮም፤ በጋልቫናይዝድ እና በተያዩ ፕሌቲንግ ሥራ የሰራ ሆኖ• በወረቀት ፋብሪካ የሠራ ወይንም በተመሳሳይ ሙያ ላይ የሠራ ቢሆን ይመረጣል

10 እስቶር ኪፐር • ዲፕሎም በሙያው ሁለት ዓመትና ከዚያ በላይ የሠራ/ች• በብረታ ብረት ፋብሪካ ውስጥ ወይንም በተመሳሳይ የስራ ዘርፍ የሰራ/ች ቢሆን

ይመረጣል

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

ከላይ የተጠቀሰውን መመዘኛ የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ መቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

አድራሻ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ከመኪና ማሰልጠኛ ወደ ሲአርቢ ሲ በሚወስደው መንገድ ወረድ ብሎ፡፡ የሥራ ቦታ - ለቁጥር 1፣2፣3፣4፣8፣9 ገላን ከተማ ስሪ ሲስተርስ ፐልፕ ፔፐርና ፓኬጂንግ ኃላ/የተ/የግ ማህበር ለቁጥር 5፣ 8፣ 7፣ 10 ቃሊቲ ገላን ብረታ ብረት ደመወዝ ---- በስምምነት የቅጥር ሁኔታ --------በቋሚነት የመመዝገቢያ ቦታ --------ገላን ብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ኬሚስት ለሁለቱም አንድ አንድ አካውንታንት ለሁለቱም አንድ አንድ ሲኒየር መካኒክ ለሁለቱም አንድ አንድ ስልክ 0114 39 20 22ፋክስ - 0114 39 20 22

Page 16: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 16

ፎቶ

አን

ተነህ

አክ

ሊሉ

ለሁሉም ሰው መኪና ለማዳረስ አቅዷል

ንግድና ኢኮኖሚ

መንግሥቱ አበበ

በላይአብ ወደ ገፅ 25 ዞሯል

ባለሀብቶቹ ሦስት ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡ የትራንስፖርትና የኮንስትራክሽን ዘርፉን በተሽከርካሪ አቅርቦት በመደገፍ፣ በሀገሪቱ ልማት የበኩላቸውን ሚና መጫወት ስለፈለጉ፣ በ1996 ዓ.ም በአራት ሚሊዮን ብር በላይአብ ኢንተርፕራይዝ ኃ.የተ.የግ.ማ አቋቋሙ፡፡ የድርጅቱን አወቃቀር በማሻሻል በ100 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል ወደ በላይአብ ሞተርስ ኃ.የተ.የግ.ማ አሳደጉት፡፡ በአሁኑ ወቅት የድርጅቱ ጠቅላላ ሀብት 230 ሚሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን በ10 ሠራተኞች ጀምሮ አሁን ከ200 በላይ ሠራተኞች እንዳሉት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍቃዱ ግርማ ይናገራሉ፡፡

የድርጅቱ ዋነኛ ተግባር፣ የተለያዩ የመኪና አካላትን ከውጭ አገር በማምጣት የተለያየ መጠን ያላቸው መኪኖችን መገጣጠም ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ፋዋ ቤላ ሴዳን (FAW Vela Seden) የተባለች የቤት አውቶሞቢል፣ የኒሳን ሞተር የተገጠመለት ባለ ሁለት ጋቢናና 3.2 ሲሲ የፈረስ ጉልበት ያለው ፒክ አፕና ኦቲንግ ስቴሽን ዋገን (ሁለቱም የመስክ መኪና) በመገጣጠም በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ እንደሚያቀርብ ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል። በተጨማሪም 16 ሜትር ኩብ የመጫን አቅም ያላቸው ፎቶን ሲኖ ትራክ ገልባጭና ከ15 እስከ 45 ኩንታል መሸከም የሚችሉ የጭነት ተሽከርካሪዎችን እያስመጣ እንደሚሸጥ ተናግረዋል፡፡ “የሥራ ዕድልና የቴክኖሎጂ ሽግግር በመፍጠር፣ እንዲሁም የውጭ ምንዛሪ በማዳን፣ ራዕዩን አሳክቷል” ይላሉ አቶ ፍቃዱ፡፡

በላይአብ ሞተርስ በአሁኑ ወቅት በአዳማ የመኪና መገጣጠሚያ፣ በአቃቂ ዋና መ/ቤትና ሾው ሩም አለው፡፡ በቃሊቲ ደግሞ ድርጅቱ ለሸጣቸውም ሆነ ከውጭ ለሚመጡ መኪኖች ሰርቪስና የጥገና አገልግሎት ይሰጣል፡፡ የመለዋወጫ ችግርም እንደሌለ የክፍሉ ኃላፊ ይናገራሉ፡፡

ባለሀብቶቹ መኪና ለመገጣጠም እንደወሰኑ በቀጥታ ወደ ሥራ አልገቡም፡፡ ከአዲስ አበባና ከአዳማ ዩኒቨርሲቲ የምህንድናስና ክፍል መምህራን ጋር በመመካከር መገጣጠም ያለባቸው የመኪና ዓይነቶችን መለየታቸውን የመገጣጠሚያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢኒያም ስነ ገልጿል፡፡ የመኪኖቹ ዓይነት ይመረጥ እንጂ ወዲያውኑ የሚያስፈልጉት ዕቃዎች መጥተው አልተገጣጠሙም፡፡ መጀመሪያ የተመረጡትን ዓይነት መኪኖች በማስመጣት ለአየር ንብረቱ፣ ለመልከዓምድሩ፣ … ተስማሚና ምቹ መሆናቸው ከታየ በኋላ ነው መገጣጠሙ የተጀመረው፡፡

“የሚገጣጠሙት መኪኖች አካላት ከቻይና የመጡ ቢሆንም ከጃፓን ጋር በሚሠሩ ኩባንያዎች የሚመረቱ በመሆኑ ጥራታቸው አስተማማኝ ነው። ለምሳሌ የቤት መኪናዎች ዕቃ የሚመጣው ከቲያንጂን ቶዮታ ኩባንያ ሲሆን ፒክአፑን ደግሞ ከኒሳን ጆንጆ ኩባንያ ነው” በማለት አቶ ቢኒያም ስለ መኪናዎቹ ጥራት ገልጿል፡፡

አሁን ግን የመስክ ፒክአፖቹን እንደ ቀድሞው ለመሸጥ ቀላል አልሆነላቸውም፡፡ ምክንያቱ

• መኪና በዱቤ እየሸጠ ነው • መኪኖችን ወደ ውጭ ለመላክና አዳዲስ

ሞዴሎች ለማቅረብ አቅዷል• የሚያሰራው ባለ 5 ኮከብ ሆቴል

ዘንድሮ ይመረቃል

በላይአብ ሞተርስ

ደግሞ የመንግሥት የሆነው ድርጅት ተመሳሳይ የመስክ መኪና መገጣጠም በመጀመሩ ነው። በፊት የመንግሥት ድርጅቶች የመስክ መኪና ለመግዛት ጨረታ ሲያወጡ፣ እየተጫረቱ ይሸጡ ነበር፡፡ አሁን ግን መንግሥታዊ የሆነው የቢሾፍቱ ኦቶሞቲቭ ኢንተርፕራይዝ ፒክአፖቹን ስለሚሠራ፣ የመንግሥት ድርጅቶች የሚገዙት ከዚያ ነው፡፡ ይህም ገበያቸውን አቀዝቅዞታል፡፡

“የቤት ኦቶሞቢሎቹ ሽያጭ ግን ከጠበቅነው በላይ ነው፡፡ የግለሰቦች የመግዛት አቅም እየተሻሻለ በመሆኑና መኪኖቹ በአንድ ሊትር 18 ኪ.ሜ በመጓዛቸው በኅብረተሰቡ ዘንድ በጣም ተወደዋል። መንግሥት፣ ቤት ለሁሉም ሰው ለማዳረስ እንዳቀው ሁሉ፤ እኛ ደግሞ መኪና ለሁሉም ሰው ለማዳረስ የዱቤ ፕሮግራም አዘጋጅተን ብዙ ሰዎች ተጠቅመዋል፡፡ ሌሎችም በዕድሉ እንዲጠቀሙ በስፋት እየሠራን ነው” ብሏል አቶ ቢኒያም፡፡

የመኪና አካላት ብዙ ናቸው፡፡ ከውጭ አገር መጥተው እዚህ በትክክል መገጣጠማቸውን የሚጠራጠሩ ሰዎች አሉ፡፡ “በኮምፒዩተር በመታገዝ ከፍተኛ የጥራት ቁጥጥር ስለሚደረግ፣ በዚህ በኩል ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ አይግባችሁ፡፡ ለዚህ ደግሞ ከእኛ መኪና ገዝተው እየተጠቀሙ ያሉ ደንበኞቻችን

እማኞች ናቸው” ይላሉ ሥራ አስኪያጁ በኩራት፡፡ ለመሆኑ እንዲህ እርግጠኛ ሆኖ ለመናገር ያበቃቸው ምን ይሆን?

“አንድ መኪና ምን ያህል ዕቃዎች እንዳሉት ይታወቃል፡፡ የታዘዙት ዕቃዎች ከአቅራቢው ድርጅት በትክክል መላካቸውን እናረጋግጣለን። በአንድ ጊዜ የሚመጣው የ36 መኪና ዕቃ ነው፡፡ ዕቃዎቹ ትክክለኛ መሆናቸውን፣ የዕቃዎቹን መጠን፣ ቁጥራቸውን፣ ለእያንዳንዱ መኪና ስንት ዕቃ እንደመጣ፣ በትክክል መግባታቸውን በኮምፒዩተር ተፈትሾ ይረጋገጣል፡፡ ከዚያ በኋላ፣ ዕቃዎቹ በሚገጠሙበት መስመር ተደርድረው ይቀመጣሉ። የዚያ መስመር ሠራተኛ ሥራ ከመጀመሩ በፊት፣ ለሥራው አስፈላጊ የሆኑ ዕቃዎች መኖራቸውን አረጋግጦ ነው ሥራ የሚጀምረው፡፡ እዚህ ላይ ሁለት ዓይነት ቁጥጥር አለ፡፡ አንደኛው የመጣው ዕቃ ጥራት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ዕቃው በትክክል መገጠሙን ይቆጣጠራል፡፡

“አንደኛው ክፍል ገጣጥሞ ከጨረሰ በኋላ በትክክል መግጠሙን ፈትሾና አረጋግጦ ነው ለቀጣዩ ክፍል የሚያስተላልፈው፡፡ ሁለተኛው ክፍልም የመጣለትን ዝም ብሎ አይቀበልም፤ በቀደመው ክፍል መገጠም ያለባቸው ዕቃዎች መኖራቸውን አረጋግጦ

ነው የሚረከበው፡፡ እሱም በተራው ለሦስተኛው ክፍል ሥራው በትክክል መጠናቀቁን ፈትሾና አረጋግጦ ያስተላልፋል፡፡ ሦስተኛውም በተራው ሁለቱ ክፍሎች እንዳደረጉት ፈትሾና አጣርቶ ለቀጣዩ ክፍል ያስተላልፋል፡፡ በዚህ ዓይነት የሚሠሩ ሦስት ስቴሽኖች አሉ፡፡ በእያንዳንዱ ስር ደግሞ ሦስት ሦስት ሳብ ስቴሽኖች አሉ፡፡ እነዚህ ሁሉ ክፍሎች በትክክል መግጠማቸውን አረጋግጠው ካሳለፉ በኋላ የጥራት ቁጥጥር (Quality control) ክፍሉ ፍተሻ ያደርጋል። ስለዚህም ምንም ዓይነት ዕቃ ሳይገጠም አያልፍም፡፡ መዘለል ብቻ ሳይሆን የአገጣጠም ስህተት እንኳ ቢኖር፣ በየክፍሉ እርምት ይደረግበታል፡፡ ስለዚህ ሦስት ጊዜ በክፍሉ፣ ከክፍሉ ሲወጣና በኳሊቲ ኮንትሮል ቁጥጥርና ፍተሻ ይደረጋል፡፡

“የዚህ ዓይነት እጅግ በርካታ (የቀለም፣ የመሪ፣ የፍሬን፣ …) ፍተሻና ቁጥጥር በየክፍሎቹና በኳሊቲ ኮንትሮል ይደረጋል፡፡ ለምሳሌ፣ መሪው ወደቀኝ ወይም ወደግራ የሚጐትት ከሆነ፣የሚፈተሽበት መሳሪያ እጅግ ዘመናዊ በመሆኑ፣ ስህተት ካለ አያሳልፍም - ቀይ ያበራል፡፡ ስህተቱ ሲስተካከል አረንጓዴ አብርቶ ያሳልፋል፡፡ ይህን ሁሉ ፍተሻና ቁጥጥር ካለፈ በኋላ ወደመጨረሻ ፍተሻ (ሬን

ፎቶ

አን

ተነህ

አክ

ሊሉ

ፎቶ

አን

ተነህ

አክ

ሊሉ

Page 17: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 17 ጥበብ

በመሆኑም ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ቀድመው ይመዝገቡ፡፡

ቅርንጫፍ በዲግሪ በደረጃ 2፣ 3፣ 4ጦር ኃይሎች

011-320-27-26

•ጤና መኮንን

•ክሊኒካል ነርስ

•ኮምፕሬሄንሲብ ነርስ •ፋርማሲ •አዋላጅ ነርስ•ላቦራቶሪ •ሳይካትሪ ነርስ

ደሴ

033-112-33-80

•ጤና መኮንን

•ክሊኒካል ነርስ

•አዋላጅ ነርስ

•ፋርማሲ

ደብረ ማርቆስ

058-771-66-

94/5

•ጤና መኮንን

•ክሊኒካል ነርስ

•አዋላጅ ነርስ

• ICT

•ሆም ኬር

•ምግብ ዝግጅትፍቼ

011-135-29-90

•ሆም ኬር

• ICT

•ግዥና ንብረት አስተዳደርጅማ

0910-58-83-37

•ሆም ኬር• ICT•ምግብ ዝግጅት•አካውንቲንግ

•ግዥና ንብረት አስተዳደር

ትሮፒካል ኮሌጅ ኦፍ ሜድስን ከተመሠረተ አስርተ ዓመታት ያስቆጠረ ሲሆን በዚህ ዘመን ውስጥ በዲግሪ፣ በዲፕሎማና በደረጃ በጤናው ዘርፍ በርካታ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ያስመረቀ ሲሆን አብዛኛዎቹ ተመራቂዎች በመንግስት መ/ቤቶች እና በግል ድርጅቶች ተቀጥረው በመሥራት ላይ ይገኛሉ፡፡

በአሁኑ ጊዜ የመንግስትን ፖሊሲ አቅጣጫ መሠረት በማድረግና ሠልጣኙ ከስልጠና በኋላ የራሱን ገቢ ማስገኛ በመፍጠር ፈጥኖ ወደ ሥራ የሚባበትን የሥልጠና መስክ በመምረጥና፣ ወደ ውጭ አገር ለመሄድ የሚያስችል ስልጠና በቅርንጫፍ ካምፓሶች ላይ ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቆ በምዝገባ ላይ ይገኛል፡፡

ትሮፒካል ኮሌጅ ኦፍ ሜድስን

ማስታወቂያ

የግጥም ጥግ

ሰሎሞን አበበ ቸኮል [email protected] [email protected]

የጮኸውን ያህል የማይናገር መጽሐፍ“ኢየሱስ ክርስቶስ በኢትዮጵያ” ሰው ነው የረቀቀ

ሰው ነው የረቀቀ ከሜርኩሪ ቬነስ፤ ከጨረቃ ከማርስከፕሉቶ ኔፕቱን፤ ኡራኑስ የላቀ ከጁፒተር ሳተርን፤ ከጣይ የደመቀ ባካባቢው ሁሉ እያሸበረቀ፤ ሰው አደገ አወቀ፤ መሬት እንቁላሉን ሰበረ መጠቀ፤ ሰው ዓለምን አየበጨለማው ቦታ ዶቃ አንፀባራቂውብ ሰማያዊ ኩዋስ፤ ሮዝ አብረቅራቂ፡፡በተጣራው አየር በነጣው ደመናባረንጉዋዴው ባህር ውሃ ተሸፍና፤ውብ ሉል ኮከብ አለም፤ የጠፈር ላይ ጤዛ፤ የሰው ልጆች እናት፤ የሰው ልጆች ቤዛ፡፡

የማታ ጀምበር ካንዱ ቤት ወዳንዱ በጣራው ተራምዳ፤ የጋራውን እናት እየነካች ሄዳ፤ እዩት ከስር ጥላው፤ የማይደርስበትን፤ እዩት ሰውን ጥላው፤ ሲለፋ ሲባክን፡፡

ገብረክርስቶስ ደስታ

መ‹ፅሐፍ ወደ ገፅ 24 ዞሯል

በአሜሪካዊ የሃይማኖት ሰባኪ እና ጥናታዊ ፊልም ሠሪ ጂም ራንኪን “ጂሰስ ኢን ኢትዮጵያ” በሚል ርእስ በአሜሪካ ውስጥ የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡ በ2005 ዓ.ም

ተተርጉመው በአማርኛ ከቀረቡ መጽሐፎችም አንዱ ነው፡፡

ብዙ አንባቢዎች የትርጉም ሥራዎችን ያለማንበብ አቋም የያዙትን ምክንያት በሚገባ ማሳየት የሚችል ከመኾኑም በላይ፤ በሀገራችን መጽሐፍን የማሳተም ሥራን በያዙት ሰዎችም የሚፈፀመውን ጥፋት አጉልቶ የሚያሳይ የትርጉም ሥራ ነው፡፡ “ኢየሱስ ክርስቶስ በኢትዮጵያ” በሚል ጯኺው ርእሱም ጭምር በብዙው ተገዝቶ ሳይነበብ አልቀረም፡፡ አሁንም በብር 40.00 እየተሸጠ ይገኛል፡፡

ይህን መጽሐፍ የግድ መመልከት ያስፈለገበት ምክንያት ቢጠየቅ “የታለ“ኢየሱስ ክርስቶስ በኢትዮጵያ የተባለው?” ለማለት ነው፡፡

አንድ አንባቢ በመጨረሻ ይህን ካልጠየቀ፣ ራንኪን በድፍረት የተናገረውን እና “ይኼ ነው ይህን የሚገልፀው ጥንታዊ የብራና መጽሐፍ” ተብሎ የተጠቆመውን በመጻፉ ብቻ በቂ ነው ብሎ ተቀብሎታል ማለት ነው፡፡ አሊያም ደግሞ፣ ለአሜሪካዊው ፀሐፊ የመንፈስ መገለጥ ብቻ አሳምኖታል ማለትም ይሆናል፡፡

በሌላ በኩል የቤተክርስትያን ሰባኪው ገና ከመነሻው ጀምሮ ሲገለጥለትና ሲገጣጠምበት የነበረውን የመንፈስ መገለጥ ምክንያት፣ ልክ ለራሱም እንደሆነለት አድርጐ በድፍኑ አምኖ ተቀብሎታል

ከማለት ሌላ ምንም አይታሰብም፡፡ራንኪንም ቢሆን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢትዮጵያ

ደርሶ እንደነበር ያሳመነው፣ በአስጐብኚው ተተርጉሞ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያ የጣና ደሴት ገዳም ውስጥ እንደጸለየ የተነገረው እና ይሄንኑ ከሚተርከው ጥንታዊ ብራና ላይ በሞባይሉ ፎቶ ያነሳቸው የጥቂት መስመሮች ትርጉም ብቻ ይመስላል፡፡ በፎቶ ያነሳትን የግእዝ ጽሑፍ አሜሪካ ውስጥ ሊያገኛቸው ለቻሉት አንድ ካህን አሳይቶ በድፍኑ ልትተረጐምለት በቃች። በመጽሐፉ ላይ እንደጠቀሰው፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ጋር ኢትዮጵያ ስለመግባቱ የሚናገር እንደሆነ ነው የነገሩት፡፡ እንግዲህ በነዚህ ብቻ ነው መግባቱን ራሱም ነው ከማለት ይልቅ በውስጣዊ መንፈሱ ሹክ እንደተባለም ሲገልፀው የነበረው፡፡ ምናልባት እሱ በቀጥታ ባይናገረው “የመንፈስ መገለጡ” ብቻ ሊሆን ይችላል ከማለት ውጭ በጭራሽ አይታሰብም፡፡

ራንኪን ኢየሱስ ከእናቱ ጋር ኢትዮጵያ መግባቱንና መቀመጡን እንዴት “ሊያውቅ” እንደቻለ የሚተርክባቸውን ገጾችና ሌሎች ተያያዥ የጉዞ ታሪኮችን እንመልከት፡፡

ጂም ራንኪን የቦብ ኮርኑክ አሣሽ ቡድን አባል ሆኖ ነው ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት የቻለው፡፡ቦብ ኮርኑክን እማናውቅ ካለን ወይም እማናስታውሰው ከሆነ፣ በኢትዮጵያ፣ አክሱም ውስጥ ታቦተ ሙሴ መኖር አለመኖሩን “በገዛ ራሴው መንገድ ላረጋግጥ” ብሎ የተነሳ ነበር፡፡ በአክሱም ጽዮን የነበረውን የቤክርስቲያን ቅርስ ጥበቃና ምዝገባ ኃላፊ ዲያቆንና ሌሎች ሁለት መነኮሳትን በረብጣ ዶላር ደልሎ፣ ጽላቱ በምሥጢር በሚቀመጥበት ገብተው እንዲመለከቱ የሞከረ ነበር፡፡ ሙከራው በሚያስደነግጥ አደጋ ተፈፀመ፡፡

ኮርኑክ ኤድዊን ፋውንዴሽን ሥራ አስኪያጅ ነው። ይህ ፋውንዴሽን የአክሱሙን እና ከዚህ በፊትም ትክክለኛዋ ሲና የት እንደነበረች ያሰሰ ድርጅት ነው፡፡

ፋውንዴሽኑ በአፖሎ ፕሮጀክት ጨረቃ ላይ በእግራቸው የቆሙና የተራመዱ ከተባሉት አንዱ

የሆነው ኤድዊን፤ ከጨረቃ ጉዞው እንደተመለሰ የመሠረተው ድርጅት ነው፡፡ ጨረቃ ላይ እግሩን እንዳሳረፈ በኅዋው ውስጥ ሽቅብ አንጋጥጦ ይቺን ምድር ባያት ጊዜ “አንዲት በቀላሉ ፍርክስ የምትል ተሰባሪ ነገር” መስላ ታየችው፡፡ ወዲያውኑ ወደ ምድር ሲመለስ ምን ዓይነት ሥራ መሥራት እንዳለበት ወሰነ፤ ኤድዊን፡፡ ድሮ ከወላጆቹ ጋር ሳለ ሲያነብበው በነበረው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጻፉ ቦታዎችንና ቅርሶችን የማሰስና የመፈለግ ሥራ፣ ይህንንም የሚሠራ ድርጅት ማቋቋም፡፡ በዚሁ መሠረት ፋውንዴሽኑን መሥርቶ ሥራውን ሲጀምር፣ በተለይም ቀዳሚው ተፈላጊ አድርጐ ያሰበውን የኖኅ መርከብ ፍለጋውን ለማካሄድ ሲነሣ የሚረዳውን ሰው ፈለገ፡፡ ትላልቅ ተራሮች ላይ ተንጠላጥሎ መውጣትን እንዲያሰለጥነውና ለደህንቱም ጠባቂው እንዲሆን በማሰብ የኮሎራዶ ፖሊስ እና ወንጀል መርማሪ የነበረውን ይህንን መቶ አለቃ ኮርኑክን ቀጠረ፡፡ እያሰለጠነው ሳለ ግን የአሠሣው ሥራም ላይ ተሳታፊ እንዲሆን ወሰነ፡፡

የኖኅ መርከብን ፍለጋው የቱርክ መንግሥት፣ አሳሾችን እንደ ሰላይ ቆጥሮ በማሰሩ ቀረ፡፡ ቀጣዩ ፕሮጀክት ሙሴ ጽላቶችን የተቀበለበት የሲናን ተራራ የት እንደሚገኝ መፈለግ ሆነ፡፡ በዚህም ላይ ኮርኑክ ከዋነኞቹ ፈላጊዎቹ አንዱ ነበር፡፡

የሲናን ፍለጋ ሥራው ካበቃ በኋላ የፋውንዴሽኑ ባለቤትና መሪ ኤድዊን ሞተ፡፡ ከዚህም የተነሳ ኮርኑክ የፋውንዴሽኑን ሥራ አስኪያጅነት ተረከበ። ታቦቱ የተሰጠበትን ሲናን እንዳገኟት፣ ያው ታቦት የት እንደደረሰ ማወቁ ደግሞ በኮርኒክ ታሰበ፡፡ እናም በቀጥታ ይገኝባታል ወደተባለችው ወደ ኢትዮጵያ ሊዘምት ተነሣ፡፡

ከዚህ በፊት እንዲሁ ስለታቦተ ሙሴ በአክሱም መገኘት፣ የታሪክ ፈለግን እየተከተለ በመመርመርና በማጥናት አክሱም ጽዮን በር ድረስ እያስረገጠ የተጓዘው ግርሃም ሃንኩክ ያቀረበውን ዘ ሳይን ኤንድ ዘ ሲል ኮርኑክ አንብቧል፡፡ “ግን አላረካኝም፣” ይል እና “ራሴ በራሴ መንገድ መፈለግ አለብኝ” ብሎ ይነሳል፡፡

ምናልባት ሃንኩክ የቃል ኪዳኑ ታቦትን ከርሱ በኋላ ለመፈለግ የሚነሳ ከመጣ፣ “እኔ ከደረስኩበት ላይ ተነስቶ አንድ ዕርምጃን ይራመድ፣” እንዳለው፣ እርሱ ከደረሰበት የሚቀጥለውን ርምጃ መራመዱ ነው ልንለው የምንችለው ዓይነት ጉዞ ነበር የተጓዘው፡፡ በገንዘብ ኃይል የመፈለግን መንገድ ነበር የመረጠው። ከዚህ ውጭ ያን ያህል የተሻለ የምርምርና የጥናት ሥራ አላደረገም፡፡

እንግዲህ፣ በዚህ ሥራ ላይ በነበረበት ጊዜ ነበር የ”ኢየሱስ በኢትዮጵያ” ጸሓፊ ኮርኑክን ያወቀው። በዚሁ የአሠሣ ሥራው በአንዱ የአሜሪካ ቲቪ ለኮርኑክ ቃለ መጠይቅ ሲደረግለት ዓይቶ ደወለለት፡፡ በመሰል ጉዳዮች ፍለጋና ዘጋቢ ፊልም በመሥራት ላይ እንደሚገኝ ገልጾ ይተዋወቃሉ፡፡

ኮርኑክ ለመጨረሻ ጊዜ የቃልኪዳን ታቦቱን ጉዳይ የሚፈጽምበትን ጉዞ ለማድረግ ሲነሳ ለጂም ራን ኪን ደውሎ፣ በዚያ ጉዞው ወደ ኢትዮጵያ ከሚጓዙት አንዱ እንዲሆን የመረጠው መሆኑን ነገረው፡፡ ሌሎች ከዚያ በፊት ይዟቸው ያልነበሩ ባለሞያዎችን ያካተተ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ ገባ፡፡

ይህ የኮርኑክ የመጨረሻ ጉዞ የፋውንዴሽኑ ባለቤት የኤድዊን መበለትም አብራ የመጣችበትና ለኢትዮጵያ መንግስት ፕሬዚዳንትም ጨረቃ ደርሳ ተመለሰች የተባለች የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማን በይፋ ማስረከብ የቻለችበት ነበር፡፡ (ያኔ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ነበሩ ፕሬዚዳንቱ)

ለኮርኑክ የመጨረሻ በሆነው በዚህ ጉዞ፣ አክሱም ላይ ለአክሱም ጽዮን የቅርስ ምዝገባና ጥበቃ ኃላፊ ሆኖ የተሾመው ወጣት በተቀበለው ረብጣ ዶላር፣ ጽላቱ ወደሚቀመጥበት ቦታ መነኮሳት እንዲገቡና እንዲመለከቱ ቢያደርግም አልተሳካለትም፡፡ አንደኛው መነኩሴ ወዲያው ሲሞት ሌላው ደግሞ ሊሞት ሲያጣጥር ነበር የቀጠሮ ቀን ደርሶ ኮርኑክ ከነቡድኑ የገባው፡፡ ኮርኑክ የሚያጣጥረውን መነኩሴ ለማግኘት ተጣደፈ፡፡ አግኝቶ አነጋገረው፡፡ በኋላ ያም መነኩሴ ሞተ፡፡ ኮርኑክ የቃል ኪዳኑ ታቦት በአክሱም መኖሩን በዚህም አረጋግጦ ነበር፡፡ ቡድኑን ይዞ ለተጨማሪ ሥራ ወደ ጣና ሐይቅ ገዳሞችም ያመራው፡፡

ጣና ከመግባታቸው በፊት ወደ ቅማንቶች በመግባት ከአንዲት ቤተ እስራኤላዊት ድድ ዘሯን በክሮሞዞም የሚመረምሩበትን ናሙና ወስደዋል።

በጣና ቂርቆስ ገዳም ውስጥ ከቤተክርስትያኑ ሕንፃ አጠገብ ከሚገኙ መቃብሮች የአንዱን አጽም በቁፋሮ ከፍተው፣ ከአጥንቱ ናሙና ለመውሰድም ጠይቀዋል፡፡ የኛን የተቀበሩትን ሰው ዘር የሚያውቁበትን ምርመራ ለማድረግ የፈለጉትን ናሙና ግን አላገኙም፡፡ በቦታው የዚያ ገዳም መሥራች እንደነበሩ የሚታወቁት መነኩሴ እንደተቀበሩበት ያውቃሉ፡፡ ነገር ግን ይህ አስቀያሚ ጥያቄአቸው በአበ ምኔቱ ሊፈቀድላቸው አልቻለም፡፡

አስጐብኚው ግን እንቢታቸውን እንዲያስለውጥላቸው በነገሩት መሠረት፣ አበ ምኔቱን አጥብቆ ይጠይቃቸዋል፡፡ አበ ምኔቱ በምንም ዓይነት እንደማይቻል በመግለፃቸው እንዳሰቡት ሳይሆንላቸው ቀረ፡፡

ከዚያ በጣና ቂርቆስ ውስጥ ያሉትን የተለያዩ ቦታዎችና አለቶች ይጐበኛሉ፡፡ በርከት ካሉት የቡድኑ አባላት ፈንገጥ እያለ፣ መንፈሱ አንድ ነገር እንደጐደለ እና እንዲፈልግ እንደሚገፋፋው አድርጐ በሚያቀርበው ገለጻው ሣር ቅጠሉን እየጠራረገ፣ በአራት እግሩ እየዳኸ፣ በአንድ ቋጥኝ ጠፍጣፋ አናት ላይ ሲያነፈንፍ የነበረው ራንኪን፤ ሳያውቀው ከደሴቱ ጫፍ ደርሶ ዥው ብሎ ሐይቁ ውስጥ ሊወድቅ እንደነበረ ገልጿል፡፡ ለጥቂት የተረፈ መሆኑን ራሱው “ኢየሱስ ክርስቶስ በኢትዮጵያ” ባለው መጽሐፉ ጽፎታል፡፡ ቋጥኙን ቧጥጦ ከሥር ውሃው ውስጥ የሚርመሰመሱት አዞዎች ቀለብ ከመሆን ዳነ፡፡

ሌሎቹ ጉብኝታቸውን ጨርሰው በመጨረሻ ከገዳሙ ከመውጣታቸው በፊት የሚያዩአቸውን ጥንታዊ ንዋያትና ቅርሶች በያዘች ያረጀች ትንሽዬ ታዛ ወርደው፣ መነኩሴው ቁልፍ ይዘውላቸው እስኪመጡ ቆመው ሲጠብቁ ጂም ራንኪን ወደ ኋላ ቀረ፡፡ አንዳች የቀረ ነገር እንዳለ ይሰማኛል” በማለት ያንን እንዲገልጽለት እዚያው ባገኘው ጠፍጣፋ ዓለት ላይ ተደፍቶ ይጸልይ ገባ፡፡

ከቤተክርስትያኑ መግቢያ አጠገብ ቆሞ እሱን ይጠብቀው ለነበረው ኢትዮጵያዊው አስጐብኚ አንድ ቄስ ይኼ ሰው የሚጸልይበት ላይ ኢየሱስም እዚህ ሳለ ይጸልይ እንደነበረ ነገረው፡፡ አስጐብኚው ይሄንኑ ለራንኪን ጮክ ብሎ ይነግረዋል፡፡ በቃ! ራንኪን የሚሆነውን ያጣል፡፡ የቀረው ነገር እንደሆነ ይሰማው የነበረውም ይኼው እንደነበረ ቅንጣት አልተጠራጠረም፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ገዳም ተቀምጦ ነው እርሱ በፀለየበት ዓለት ላይ ዘወትር “ከአባቱ ከእግዚአብሔር አብ ጋር ይነጋገር የነበረው፡፡” እንዲያውም እሱ እንደገለጸው፤ “ኢየሱስ ከእግዚአብሔር አብ መመርያን ይቀበል ነበር፡፡”

በዚህ ነገር ራንኪን በኃይለኛ ስሜት ውስጥ ገብቶ ሳለ፤ ይኼን በዝርዝር የሚናገረውን መጽሐፍ ደግሞ እታች እንደሚያገኙ አስጐብኚው በነገረው መሠረት ወደዚያው ተጣድፎ ይወርዳል፤ ሌሎቹ አባላቱ ቆመው በሚገኙበት፡፡

ካህኑ ይዘውት በመጡት መክፈቻ በከፈቷት ትንሽዬ ደሳሳ አሮጌ ቤት ውስጥ በኦሪት ዘመን መስዋዕት ይቀርብባቸው የነበሩ ንዋያት፣ ካህኑ ይለብሱት የነበረው፣ እንዲሁም ሁለት መለከቶችን ጭምር ያሳዩአቸዋል፡፡

Page 18: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 18 ጥበብ

ማስታወቂያ

ወልደመድህን ብርሃነ መስቀል

ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው

“የሕልም ሩጫ” የቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸውን የሕይወትና ታሪክ የሚያስቃኝ መጽሐፍ ሲሆን በ1949 ዓ.ም ነው የታተመው፡፡ በባለታሪኩ ተዘጋጅቶ የቀረበው መጽሐፍ መገረምን የሚፈጥሩ ብዙ ጉዳዮችን ይዟል፡፡

መጽሐፉ በ130 ገፆች የተቀነበበ ቢሆንም የጥራዙ ሁለት ሦስተኛ ገፆች በፎቶግራፍና ስዕሎች የተሞላ ነው፡፡ መጽሐፉ በቁም ጽሕፈት የተዘጋጀ ሲሆን የያዘው ቁም ነገር በትምህርት፣ በሥራ ልምድና በዕድሜ ብዙ ዕውቀት ከቀሰመ ሰው የመነጨ ስለመሆኑ ማንም ሊመሰክርለት የሚችል ነው፡፡ ታሪኩን እንደሚከተለው አሳጥሬ ላቀርበው ሞክሬያለሁ፡፡

በ”የሕልም ሩጫ” ሲታወሱ

በ1895 ዓ.ም በ12 ዓመቴ ከአዲስጌ አዲስ አበባ መጥቼ ከዚህ ዓለም እሽቅድምድም ገባሁ። አንዱ ሲሾም ሌላው ሲሻር፣ አንዱ ሲታሰር ሌላው ሲፈታ፣

አንዱ ሲሞት ሌላው ሲተካ በማየት የዚህን ዓለም እሽቅድምድም ትግል አጠና ነበር፡፡ በ1895 ዓ.ም የምኒልክ ትምህርት ቤት ሲከፈት (ትምህርት ቤቱ 4 ኪሎ ከመምጣቱ በፊት ፒያሳ በአልፍሬድ ኤግል

መኖሪያ ቤት እያለ ማለታቸው ይሆናል) ደጃዝማች ተፈሪ መኮንን፣ ልጅ ብሩ ሃብተማርያም፣ እምሩ ኃይለሥላሴ፣ ዘውዴ ጐበና፣ አስፋው በንቲ፣ እኔና ሌሎች ልጆችም አብረን ነበርን፡፡

የአጐቴ ሞት ጥልቅ ሀዘን ላይ ስለጣለኝ 5 ዓመት በጽሞናና በብቸኝነት ተቀመጥኩ፡፡ “ፍላጐትህን ስታባርረው ተመልሶ እየጋለ ይመጣል” እንደሚባለው እሽቅድምድሙን ዓለም ተመልሼ ተቀላቀልኩ፡፡ በዚያ ዘመን ተወዳዳሪን ለማሸነፍ የቤተ - መንግስትን ሥርዓት ማወቅ ያስፈልግ ነበር፡፡ ባለማዕረግ አባት የሞተበት ልጅ በቀላሉ ወደ ስልጣን ይወጣል፡፡ እኔ አባቴ በልጅነቴ ስለሞተ ውድድሩን በጥረቴ ማሸነፍ ነበረብኝ፡፡ አፄ ምኒልክ ከሞቱ በኋላ ከልጅ ኢያሱ ጋር መግባባት ስላልቻልን ይኸም ተጨማሪ መከራ ሆነብኝ፡፡ ባለመሾሜ እኔ ብቻ ሳልሆን ወዳጆቼም ሀዘን ገባቸው፡፡ አለቃ ገብረሚካኤል ለሚባሉ አባት ጭንቀቴን ስነግራቸው:-

“አንድ ወዳጅህ የሆነ ሰው ምሳ ቢጋብዝህ ቁርስ ለመብላት ትሄዳለህን ወይስ ለራት ቢጋብዝህ ለምሳ ትሄዳለህ? እንደዚሁም ሁሉ እግዚብሔር በዚህ ዓለም ለሥራ የመረጠውን ሰው አንዳንዱ በጠዋት፣ አንዳንዱን በእኩለ ቀን፣ ሌላውንም በማታ ነው የሚጠራው፡፡ ምናልባት አንተ ለእኩለ ቀን ወይም ለማታ ተጠርተህ እንደሆን፤ ለጠዋት ካልሆነህ ብለህ በከንቱ ታዝናለህን?” አሉኝ፡፡ ምክራቸው ልቤን ነካኝ፡፡ እኔም ደጅ ጥናቱን ትቼ ቤቴ ተቀመጥኩ፡፡

በምኒልክ ትምህርት ቤት አብረውኝ የተማሩት ልጅ፤ አልጋ ወራሽ ሲሆኑ አለቃ ገብረሚካኤል የሰጡኝ ምክር ትዝ አለኝ፡፡ በወዳጄ ዘመነ መንግስት ከአስር የማያንሱ የስልጣን ማዕረጐችን አገኘሁ፡፡ በአገር ውስጥና ከአገር ውጭም በተለያዩ ኃላፊነቶች እየተሾምኩ አገለግልኩ፡፡ በ1921 ዓ.ም በለንደን ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆንኩ፡፡ በማይጨው

ጦርነት ከንጉሱ ጋር አብሬያቸው ነበርኩ፡፡ ሚያዝያ 24 ቀን 1928 ዓ.ም ከኦጋዴን ጦር ሜዳ በጅቡቲ በኩል ወደ አውሮፓ ሲሄዱም በቅርብ ነበርኩ፡፡

በ1907 ዓ.ም የራስ ቢትወድድ መንገሻን ልጅ ዘውዲቱን አግብቼ ሰላምና ደስታ የሞላበት ትዳር ነበረኝ፡፡ ከጃንሆይ ጋር ወደ ውጭ በሄድኩበት ወቅት ታምማ አልጋ ላይ ነበረች፡፡ ዳግመኛ መገናኘት አልቻልንም፡፡ ሁለተኛው ትዳሬን የመሠረትኩት በኢየሩሳሌም ሲሆን ልዕልት የሻሽ ወርቅ ይልማን ነው ያገባሁት፡፡ በስደት ላይ እያለንም የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ተወካይ ሆኜ ወደተለያዩ አገር ባለስልጣናት እየሄድኩ ጉዳይ አስፈጽሜያለሁ ጠላት በተባረረ ማግስት በ1934 ዓ.ም የአገር ግዛት ሚኒስቴር ሚኒስትር ሰብሳቢ ሆንኩ፡፡ በኢሊባቡር ጐሬ ተሹሜም ሠርቻለሁ፡፡ መፃሕፍትን መፃፍ የጀመርኩት እንደትርፍ ጊዜ ሥራ ነበር፡፡ ይህን “የሕልም ሩጫ” ብዬ የሰየምኩትን መጽሐፍ ያዘጋጀሁበት ምክንያት ሰው በነፍሱ አፈጣጠር ከፍ ያለ መሆኑን፤ በሥጋዊ አፈጣጠሩ ብልሹ መሆኑን ለማሳየት ነው፡፡

እግዚአብሔር ባንዱ እጁ አንዱን ዘመን ሲያጠፋ፣ በሁለተኛ እጁ ሌላውን ዘመን ያበራል። እድሜና ዘመን ከመሄድ አያቋርጡም፡፡ ሰውም የጊዜው ተገዢ በመሆኑ በሰከንድ፣ በደቂቃ፣ በሰዓት፣ በቀን፣ በወርና ባመት ላይ ተቀምጦ ይገሰግሳል፡፡ ማንም ባለስልጣን ሰው ቢሆን ነገን ጠልቸዋለሁና ልለፈው፤ ትላንትን ወድጄዋለሁና ልመልሰው ለማለት አይችልም፡፡ ስለዚህ በራስ ሃሳብና ምኞት መጣደፍ የሕልም ሩጫ፣ የማይጨበጥ አረፋ ይሆናል፡፡

የሰው ልጅ እንዳትክልት በሕፃንነቱ ለምልሞ፣ በወጣትነቱ አብቦ፣ በጐልማሳነቱ አፍርቶ ሲታይ ደስ እንደሚል እንደዚሁ በዕድሜ ጠውልጐ፣ በእርጅና

ደርቆ፣ በሞት ሲቆረጥ የሰውን የመጨረሻ ዕድሉን ስናስበው በጣም ያስገርማል፡፡ ይህ ሲታይ ሰው በዚህ ዓለም ላይ ለጥቅምና ለክብር የሚደክመውና የሚሮጠው ሁሉ የሕልም ሩጫን ይመስላል፡፡

በስደት ላይ ሳለን ሥዕሎችንም እስል ነበር፡፡ ነፃነት ተመልሶ በአገራችን መኖር ስንጀምር ባለቤቴ ልዕልት የሻሽወርቅ ይልማ ሕፃናት መርጃ የበጐ

ሩጫ ወደ ገፅ 21 ዞሯል

ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው

Page 19: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 19 ጥበብኪነጥበባዊ ዜና

መልካሙ ተክሌ

አጭር ልብወለድ

ከምሽቱ አንድ ሰዓት በመሆኑ የአራት ኪሎ ጉራንጉሮች በደንበኞቻቸው መጨናነቅ ጀምረዋል። ሰካራሙ፣ ወፈፌው፣ ቅንዝራሙ፣ መንታፊው፣ ለፍላፊው፣ ሴተኛ አዳሪዋ፣ ወንድ አዳሪው፣ ሎተሪና ቆሎ አዙዋሪው…የአራት ኪሎ ጉራንጉሮች ቁዋሚ ደንበኞች ናቸው፡፡ መንገዱም፣ ቤቱም፣ ድንግዝግዝ ያለ ነው - በአራት ኪሎ ሸለቆዎች፡፡

በአራት ኪሎ ጉራንጉሮች ውስጥ ሀፍረት፣ ይሉኝታ፣ ባህል፣ እምነት…እምብዛም ቦታ ያላቸው አይመስሉም፡፡ ስርቆት፣ ዝሙት፣ ቅጥፈት፣ ውስልትና…የጉራንጉሮቹ መገለጫዎች ናቸው፡፡ አራት ኪሎ፤ ሞቃ፣ ግላ፣ ልትቀልጥ የምትደርሰው አመሻሽ ላይ በመሆኑ፤ ሲመሽ የነጋ፣ ሲነጋ ደሞ የመሸ ይመስላል፡፡ መንገዶችዋ የተጨናነቁ ናቸው፤ ኑሮ የተጨናነቀ ነው፡፡ ቤቶችዋ እጅግ የተጨናነቁ ከመሆናቸው የተነሳ፣ የሰው ሳይሆን የወፍ ጐጆ ይመስላሉ፡፡ የቤት ወጉ ሳይኖራቸው ቤት ተብለው ሰው ከሚኖርባቸው ውትፍትፍ ጐጆዎች አንድዋ የሃዳስ ገብሩ ክፍል ናት፡፡

የሃዳስ ክፍል፣ የተመረገችበት ጭቃ ወላልቆ በመውደቁ፤ በቡትቶ፣ በካርቶን እና በስሚዛ ቅጠል ተወታትፋ ላስተዋላት፣ ለሰው ሳይሆን፣ ለውሻ ማደሪያነት እንኩዋ፣ ብቃት የሌላት ትመስላለች፡፡ ክፍልዋ፣ ውስጥዋም እንደ ውጭዋ የተጐሳቆለ ነው።

ከአንድ የረጥባ አልጋና ከእንጨት ሳጥን በቀር ሌላ ንብረት አይታይም፡፡ ሳጥንዋ፣ የልብስ ማስቀመጫም ወንበርም ናት፡፡ ከሳጥኑ ጀርባ፣ በኮምፔልሳቶ የተጋረደች እጅግ ጠባብ ክፍል አለች - ጥቂት የሻይ ብርጭቆዎችና ባዶ የአረቄ ጠርሙሶች የሚቀመጡባት፡፡

ሀዳስ፤ እምብዛም ውብ፣ እምብዛም መጥፎ ያልሆነውን ጭንዋን በአግባቡ የሚያሳይ አጭር ጉርድ ቀሚስ ለብሳ፣ አምባሬጭቃዋን ተባብሳ፤ አንዴ ጐርደድ፣ እንደገና ቀጥ እያለች፣ እየተሽኮረመመች፣ እያሽኮረመመች፣ አላፊ አግዳሚውን ለመጥለፍ ያደረገችው ሙከራ አልሳካላት ስላለ፣ ደከማትና ወደ በርዋ ተመለሰች፡፡ “ምን አይነት ነጃሳ ቀን ነው? አስራ ሁለት ሰአት ሳይሞላ የወጣሁ እስከ አንድ ሰአት ድረስ እንዴት አንድ ሰካራም እንኩዋ አጣለሁ? ፎጋራ ቀን…” ባይሰማትም ምሽቱን ሰደበችው፡፡

በርዋን ተደግፋ ቆማ፣ የሰፈርዋን ሴቶች ስታይ፣ አንዳንዶች ከደንበኞቻቸው ጋር ቆመው “ዋጋ ጨምር፣ ቀንሽ” ይወጋወጋሉ፤ የቀናቸው፣ ይዘው ይገባሉ፡፡ ቀደም ብለው ያስገቡም፣ ቶሎ ብለው አስወጥተው፣ ሌላ ለመጥለፍ ይሽቀዳደማሉ፡፡

ሌሎች፣ እንዲህ አይነት እድል ሲገጥማቸው፣ እስዋ ለምን እንደሚጠምባት እያሰላሰለች፣ በጉዋደኞችዋ እየቀናች ሳለ፣ ጐረቤትዋን ሲያነጋግር የነበረ አንድ ጐረምሳ በአጠገብዋ ሲያልፍ አየት አረጋት፤ ጠቀሰችው፡፡ ዋጋ ጠየቃት፤ ነገረችው። ተስማሙ፡፡ ተከትሎዋት ገባ፡፡ ሞከረ፣ ግን፣ ሰውነቱን የሆነ ነገር ቀፈፈው፡፡

“ታረጋለህ አርግ፤ አለዚያ ውረድልኝ ሰውዬ” ሀዳስ ድንገት አንባረቀችበት፡፡

“ቆይ በእናትሽ? ስሜቴን አትዝጊው…” ኤፍሬም በማባበል ስሜት ጠየቃት፡፡

“ስሜት? እንዲህ አርጐም ስሜት የለ…” የሽሙጥ ሳቅ ሳቀችበት፡፡

“እንዴት ስሜት የለኝም!”“ስሜት ታለህ ታዲያ ምን ያልፈሰፍስሃል?”

በንቀት አየችው፡፡ “ማን ነው ልፍስፍስ?”“እኔ ልበልህ ወንድም? ለጭቅጭቅ ጊዜ የለኝም፤

ከቻልህ አርግ፤ ካልሆነልህ ደሞ ውረድ” መረር አለችበት፡፡

“በእናትሽ አባብይው?”“እ…? አባብይው? ማሙሽዬ አይዞህ … ባባ ኬክ

ይዞልህ ይመጣል ልበለው?”ምስኪንዋ ጐጆ እስከምትሰነጠቅ ሳቀችበት፡፡

በኦርዮን ወ/ዳዊት

“ቢዝነሱ”

“በእናትሽ? ትንሽ ሞክሪ?” ድጋሚ ተማፀናት፡፡ “ውረድ ልፍስፍስ…”“ለምን ነው የምወርድ?”“እና አዝየህ ላድር ነው? በቢዝነስ ቀልድ የለም፤

ይገባሀል?”“ቢዝነስ? የቱ ነው ደሞ ያንች ቢዝነስ?”“ሚስትህ መሰልሁህ? እየሰራሁ ያለሁትኮ

ቢዝነስ ነው”“ኧ…ሽርሙጥና በበረሃ ስሙ ሲጠራ ነው ቢዝነስ

ማለት?” ኤፍሬም የፌዝ ሳቅ ሳቀባት፡፡ “በበረሃም ጥራው በደጋ ስሙ፣ ለኔ ቢዝነሴ

ነው። ልቀቀኝ” ቀኝ እግርዋን ከራቁት ገላው ላይ አነሳች፡፡

“አንቺ እንቢ ካልሽ፣ ጉዋደኛሽን አላጣት፤ ምን ቸገረኝ፡፡ ብሬን መልሽልኝ”

“የምን ብር?” ተኮሳተረችበት፡፡ “የሰጠሁሽን አምስት ብሬን ነዋ”“ኧረ ባክህ? እስካሁን ስታለፋኝ የቆየህ ያባትህ

ቅሬላ መሰልሁህ” ኤፍሬም ተኝቶበት የነበረውን ግራ እግርዋን ለማስለቀቅ ታገለችው፡፡ ማንም እየመጣ ሲጨፍርባት የተሰላቸችው የረጥባ አልጋም አብራት ተነጫነጨች፡፡ “ልቀቀኝ ብዬሃለሁ ሰውዬ! ሁዋላ ትዋረዳለህ”

“ምን አባትሽ ልትሆኝ? ጥንብ ሸርሙጣ…” ኤፍሬም መልሶ ደፈቃት፡፡

“ሽርሙጥናዬን ፈልገህማ ነው የመጣኸው፤ ስብሰባ የተጠራህ መሰለህ? ባለጌ ልፍስፍስ! ወንድ ሆኜ ያንተን ድርሻ ላረግልህ ትፈልጋለህ? ሙትቻ! ወንድ ከሆንህ ያውልህ አርግ?” በጣትዋ ወደ ጭኖችዋ መሀል ጠቆመችው፡፡

ኤፍሬም የበታችነትና የመጠቃት ስሜት መላ አካላቱን ሲወርረው ተሰማው፡፡ እናም፣ ድንገት በጥፊ አጮላት፡፡ ሃዳስ፣ እየጮኸች እንደድመት ትቡዋጭረው ጀመር፡፡ እንደምንም ገፍትሮ ወደ አልጋዋ ጫፍ ጣላትና በችኮላ፣ ሱሪውን ከጣለበት ሳጥን ላይ ቢፈልገው አጣው፡፡

“ሱሪዬን የት አባትሽ ነው የደበቅሽው?”“እበት ብላ! ጅል የወንድ አልጫ! ደሞ አንተ ምን

ሱሪ አለህ?”

ኤፍሬም እንደ ገና በጥፊ ሲያልሳት፣ አራት ኪሎን በጩኸት አደበላለቀችው፡፡ ወዲያው፣ የሃዳስ ክፍል ወደ ሲኦልነት የተቀየረች መሰለች፡፡ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ፣ ምክንያቱን ያወቁትም ያላወቁትም፤ ብቻ የወሬ ሱስ ያለባቸው የአራት ኪሎ ሴትኛ አዳሪዎች፣ ጩኸቱንም ግርግሩንም እያባባሱት መጡ፡፡

ከአካባቢው የማይጠፉት የፖሊስ አባላት ግን፣ “የተለመደ የቁራ ጩኸት ነው” በማለት ነገሩን ችላ ብለውት ነበር፡፡ ሆኖም፣ ሃዳስ ቤት ሰው መገደሉን የስሚ ስሚ ሲሰሙ፣ በቸልታቸው ተፀፀቱና አካባቢውን በፍጥነት ተቆጣጠሩት፡፡

ፖሊሶች፣ ጩዋሂዋንም፣ አጩዋጩዋሂውንም እየገፈተሩ ከሃዳስ በር ሲደርሱ፣ ኤፍሬም ከወገቡ በታች እንደተራቆተ፣ እንጨት ሳጥኑ ላይ በአፍጢሙ ተደፍቶ፣ ደም እንደጐርፍ ሲወርደው አዩ፡፡

ሁለት የፖሊስ አባላት የኤፍሬምን አስከሬን በአንቡላንስ ይዘው፣ ወደ ምኒልክ ሆስፒታል ሲከንፉ፣ ሌሎች ግን፣ ወንጀለኛውን ለመያዝ፣ አራት ኪሎን ያተራምሱዋት ጀመር፡፡ ብዙም ሳይቆዩ፣ በርካታ ተጠርጣሪዎችን በመያዝ ወደ ጣቢያቸው ተመለሱና፣ የተለመደውን ምርመራ ቀጠሉ፡፡ ብዙዎችን የያዙዋቸው ቀድሞውንም ለማስረጃ ያህል ስለነበር፣ እንደነገሩ እየጠያየቁ፣ ወደ መቆያ ክፍል ላኩዋቸው፡፡ “ገዳዩ እሱ ነው” ተብለው በጥቆማ ከያዙት ዋናው ተጠርጣሪ ላይ ግን፣ ምርመራቸውን ጠበቅ አደረጉ፡፡

“ስም?” መርማሪ ፖሊሱ ጠየቀ፡፡ “የሰፈር ስሜን ነው ወይስ ዋናውን?”“መ..ጀመሪያ የሰፈሩን ንገረኝ”“ብዙ ነው”“ለምሳሌ?”“አሞራው፣ እ…ገንድስ፣ ቆሪጥ፣ አጅሬው፣

እ…ሌላም ይሉኛል፡፡ ግን ይኸ ሁሉ ለአንተ ምን ያረግልሃል?” ተጠርጣሪው መርማሪውን ጠየቀው፡፡

“ሌላ ማን ይሉሃል?” መርማሪው ያልሰማ መስሎ ጠየቀው፡፡ “አፍን”

“ሌላስ?”

ቢዝነሱ ወደ ገፅ 23 ዞሯል

ሰሜን ሸዋ የቱሪዝም ማጣቀሻ አሳተመ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ የሰሜን ሸዋ ዞን፡ የቱሪዝም መስሕቦች ማጣቀሻ ዳይሬክተሪ አሳተመ፡፡ ከሐገሬ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ጋር በመተባበር ዞኑ ያሳተመው ዳይሬክተሪ፤ የአካባቢውን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መስሕቦች ዝርዝር የሚያካትት ነው፡፡ በአማርኛ ብቻ የተዘጋጀው ዳይሬክተሪው፤ የእንግሊዝኛና ፈረንሳይኛ ቅጂ በቅርቡ እንደሚዘጋጅለት ለማወቅ ተችሏል፡፡ ዞኑ ከያዛቸው ታሪካዊ ቅርሶች መካከል በጥንቷ ልቼ ከተማና በአንኮበር የሚገኙ የዳግማዊ አፄ ምኒልክ አብያተ መንግስት ይገኙበታል፡፡ የቱሪዝም ዳይሬክተሪው የዛሬ ሳምንት ይመረቃል ተብሏል፡፡

“የኛ” ልጆች ዛሬ በባሕር ዳር የሙዚቃ ድግስ ያቀርባሉየሴቶችን አቅም ለማሳደግ ያለሙ ዝግጅቶች በሸገር

ኤፍኤም እንዲሁም በአማራ ክልል ሦስት ኤፍኤሞች እያቀረበ ያለው “የኛ” የሬዲዮ ፕሮግራም፤ ዛሬ በባሕርዳር ስቴዲየም የሙዚቃ ድግስ ያቀርባል፡፡ ከቀኑ ሰባት ሰአት ጀምሮ በባሕርዳር ስቴዲየም ለሕዝብ በነፃ የሚቀርበው የሙዚቃ ድግስ በዋነኛነት በልጃገረዶቹ የሙዚቃ ቡድን ይደምቃል፡፡ የልጆገረዶቹ የሙዚቃ ቡድን፤ ከአንጋፋዋ ዕውቅ ድምጻዊት አስቴር አወቀ ጋር ያዘጋጀውን የሙዚቃ ክሊፕም በቀጣዩ ወር ይለቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ “የኛ” ልጆች ያዘጋጁት ‘አቤት’ ነጠላ ዜማ ባለፈው ሳምንት “ምርጥ ነጠላ ዜማ” ተብሎ በሸገር ኤፍ ኤፍም የ “ለዛ” ፕሮግራም መሸለሙ ይታወሳል፡፡

“የተወጠረ ገመድ” የሥዕል አውደርእይ ዛሬ ይከፈታል

“የኢትዮጵያ ባሕላዊ ሥዕል ኤግዚብሽን ተከፈተ

በሠዓሊ ኤልያስ ሥሜ የተዘጋጁ የሥዕል ሥራዎች የሚቀርቡበት “የተወጠረ ገመድ” የሥዕል ዐውደርእይ ዛሬ በብሪቲሽ ካውንስል የሚከፈት ሲሆን አውደርዕዩ በጎተ ኢንስቲቲዩት፣ በአሊያንስ ኢትዮፍራንሴና በጣሊያን የባሕል ተቋም እንደሚቀርብም ታውቋል። የስዕል አውደርዕዩ በመስከረም አሰግድ ኩሬተርነት የሚቀርብ ነው፡፡ ሰዓሊ ኤልያስ ሥሜ ካሁን ቀደም በግሉ ዘጠኝ ዐውደርእዮች በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ያቀረበ ሲሆን ከሌሎች ሠዐሊያን ጋር ደግሞ ስድስት ዐውደርእዮች አቅርቧል፡፡

በሌላም በኩል “የኢትዮጵያ ባሕላዊ የሥዕል ኤግዚብሽን” ከትናንት በስቲያ በላፍቶ አርት ጋለሪ ተከፍቶ መታየት እንደጀመረ ጋለሪው አስታወቀ። ሳር ቤት ብስራተ ገብርኤል ቤተክርስትያን አካባቢ የተከፈተው ዐውደርእይ፤ አስር ሠዐሊያንን ያሳተፈ ሲሆን እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2006 ዓ.ም ለሕዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል።

“በፍቅር ላይ ሾተላይ” እና “የተወጋ ልብ” የተሰኙ ሁለት መጻሕፍት ነገ ከጧቱ 2፡30 በብሔራዊ ትያትር እንደሚመረቁ ዳኒ ሮጐ የማስታወቂያና ፊልም ፕሮዳክሽን አስታወቀ፡፡ በደራሲ ትክክል ገና የተፃፉት ሁለት የረዥም ልቦለድ መጻሕፍት በ2004 እና በ2005 የታተሙ ናቸው። በእውነተኛ ፍቅር ላይ ተመስርቶ የተፃፈው “የተወጋ ልብ”፤ 256 ገፆች ያሉት ሲሆን ዋጋው 40 ብር ነው፡፡ “በፍቅር ላይ ሾተላይ” 238 ገፆች ያሉት ሲሆን በተመሳሳይ ዋጋ ለገበያ ቀርቧል፡፡

በተያያዘ ዜና ዊዝ ኪድስ ዎርክሾፕ፤ “ፀሐይ መማር ትወዳለች” የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ድራማ እንዲሁም የልጆች መጻሕፍትን ዛሬ ከጧቱ 3 ሰዓት እንደሚያስመርቅ አስታወቀ፡፡ በብሔራዊ ቤተመጻሕፍትና ቤተመዛግብት አዳራሽ የሚመረቁት ድራማና መጻሕፍት ዕድሜአቸው ከ3 እስከ 9 ዓመት ላሉ ሕፃናት የተሰናዱ ናቸው፡፡ ዊዝ ኪድስ ዎርክሾፕ የተለያዩ ዓለምአቀፍ ሽልማቶች እንደተሸለመ ይታወቃል፡፡

በሌላም በኩል “ቶላ አባ ፈርዳ” የተሰኘው የኮሜዲያን አስረስ በቀለ የሕፃናት መጽሐፍ ከትናንት በስቲያ ጧት አለምገና በሚገኘው አንኮር ሆቴል መመረቁን ስፖት ላይት የትምሕርት ማበልፀጊያ ማዕከል አስታወቀ፡፡ ኮሜድያን አስረስ ለአስራ ሁለት ዓመታት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የልጆች ፕሮግራም ላይ በትወና፣ በድርሰት ጽሑፍ እና በአዘጋጅነት የሠራ ሲሆን “የቼሪ ማስታወሻ” እና “የአቶ በላቸው ጫማ” በተሰኙት የልጆች መጻሕፍቱም ይታወቃል፡፡

“በፍቅር ላይ ሾተላይ” እና “የተወጋ ልብ’” ነገ ይመረቃሉ የኮሜዲያን አስረስ

በቀለ የሕፃናት መጽሐፍ ተመረቀ

“ፍቅሬን ያያችሁ” ፊልም ሰኞ ይመረቃል

የደራሲና ዳይሬክተር ሱራፌል ኪዳኔ “ፍቅሬን ያያችሁ” ፊልም የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 11 ሰዓት በብሔራዊ ትያትር እንደሚመረቅ ወርቅ ሚዲያ ፕሮዳክሽን አስታወቀ፡፡ ለመሥራት አንድ ዓመት በፈጀው ፊልም መሐመድ ሚፍታ፣ ሩት አርአያ፣ እንግዳሰው ሀብቴና ሌሎችም ተውነዋል፡፡

Page 20: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 20 ጥበብ

አበባየሁ ገበያው

ባለፈው ሳምንት አሜሪካ በነበርኩበት ጊዜ በላስቬጋስ የታወቀ ሆቴል ውስጥ የፋሺን ዲዛይን ስራዎቿን ስታቀርብ ያገኘኋትን ፍሬህይወት

የተባለች ኢትዮጵያዊ ዲዛይነር በቃለ ምልልስ መልክ አስተዋውቄአችሁ ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ በኒው ኦርሊንስ፣ ጃክሰን ጐዳና ላይ ከበርካታ ዝነኛ ሠዓሊያን ጋር ሥዕል ሲስል ያገኘሁትን ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አስተዋውቃችኋለሁ፡፡

ሠዓሊ ተስፋዬ ንጉሴ ይባላል፡፡ የተወለደው ወንጂ ነው፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ሲያጠናቅቅ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ የሥነጥበብ ት/ቤት በመግባት ለ5 ዓመት የሥዕል ትምህርት ተከታትሏል፡፡ ከዚያም “ኤርታሌ” የተባለ ስቱዲዮ ከፍቶ በሥዕል ስራ ላይ ተሰማራ፡፡ በሥዕል ስራ ገንዘብ ማግኘት የጀመረው ግን የ9ኛ ክፍል ተማሪ እያለ እንደሆነ ተስፋዬ አጫውቶኛል። በሥዕል ትምህርት ድግሪውን ከወሰደ በኋላም ለበርካታ የግል ጋዜጦችና መጽሔቶች ካርቱኖችን ይሰራ ነበር። የዛሬ ስድስት ዓመት ገደማ ነው ነፃ የትምህርት ዕድል አግኝቶ ወደ አሜሪካ ያቀናው፡፡ በዚያው አሜሪካ ቀረ፡፡

በጃክሰን ጐዳና በሥዕል ስራው ላይ ተጠምዶ ሳየው ላነጋግረው ፈለግሁና ቀጠሮ ያዝኩኝ፡፡ በቀጠሮአችን ዕለት መኖሪያ ቤቱ ውስጥ ወዳለው የስዕል ስቱዲዮው ይዞኝ ሄደ፡፡ ገና መኖሪያ ቤቱ ስገባ “ትክክለኛ የሠዓሊ ቤት” አልኩኝ-ለራሴ። ቀለም … ብሩሽ … የስዕል ሸራ … የተለያዩ ሥዕሎች … ኮምፒውተር…የቀለጠ የሻማ ተራራ… ተመለከትኩኝ። በቀጥታ ወደ ቃለምልልሱ አልገባንም፡፡ ተስፋዬ ወጥቤት ገብቶ ምግብ ማሰናዳት ጀመረ፡፡ ሠዓሊነትና የምግብ ዝግጅት ሙያ ግንኙነት ይኖራቸው ይሆን? ብዬ እያሰብኩ ነበር ያሰናዳውን ምግብ ይዞ ከተፍ ያለው፡፡

ምግቡ ምን እንደሚባል ባላውቀውም በጣም ወድጄዋለሁ፡፡ ቅጠላ ቅጠል የበዛበት ምግብ ነው። ጣዕሙ ልዩ ነው፡፡ አቀራረቡ ይማርካል፡፡ እንደ ሥዕል በህብረ ቀለማት የደመቀ ነው፡፡ የምግቡን ስም ማወቅ ፈለግሁና ተስፋዬን ጠየቅሁት፡-

ምንም ሆነ ምን አንዴ በልተሽዋል፡፡ እንዳየሁሽ ደግሞ ወደሽዋል፡፡ ለጊዜው ግን ስም አልወጣለትም። የእኔ ፈጠራ ነው፡፡

(ከምግብ በኋላ እሱ ሸራው ላይ እየሳለ፣ እኔም ቃለመጠይቁን ጀመርኩ፡፡)

እንዴት ነው አሜሪካ ለሥዕል ስራ ትመቻለች?አሜሪካኖች የፈጠራ ስራን በጣም ያከብራሉ።

የሥዕል ስራዎችን በብዛት ይገዛሉ፡፡ ጃክሰን ስኩዌር (ጐዳና) አላየሻቸውም… ምን ዓይነት ሰዎች እንደሚመጡ? ሥዕል የሚገዙ አይመስሉም…ቱሪስቶች ናቸው፡፡ ግን ይገዙሻል፡፡ ጃክሰን ስኩዌር ትላልቅ ሥዕሎችን ይዞ ለመቀመጥ ቦታው አመቺ አይደለም፡፡ ትናንሽ ሥዕሎችን እየሰራን ነው የምንሸጠው፡፡ አንዱ ሥዕል ከ250-800 ዶላር ነው የሚሸጠው፡፡

ከሥዕል ስራ ውጭ የህንዶች ሱቅ ውስጥ ተቀጥሬ ማታ ማታ እሰራለሁ፡፡ በተረፈ ሥዕሎቼን በየመደብሩ እየዞርኩ አከፋፍላለሁ፡፡ ሰው የሚወዳቸውን ሥዕሎች እየሰራሁም አሳትሜ አዘጋጃለሁ፡፡ ቅዳሜና እሁድ ደግሞ ጃክሰን ስኩዌር ሄጄ ከሠዓሊዎቹ ጋር እሰራለሁ፡፡ ዝም ብለው ተራ ሠዓሊዎች እንዳይመስሉሽ፤ ዓለም አቀፍ ሰዓሊያን ናቸው፡፡

በሥዕል ሽያጭ ከብረሃላ?ደሞ አገር ቤት ወዳጅ ዘመድ ሃብታም ሆኗል

ብለው ያስቸግሩኛ! አየሽ…ፈጠራ ከተከበረ ልብሽም ይረጋጋል፡፡ እየተመሰጥሽ ፈጣሪንና አለምን አገናኝተሽ ቁጭ ነው፡፡ ሃብታም ሆነሃል ነው ያልሽው? ቆይ ሃብታም ነኝ እንዴ? ይመስገነው…በአለም መድረክ የአገሬን ስም ማስጠራት ችያለሁ። ከእውቅ ኢትዮጵያውያን አንዱ ሆኛለሁ፡፡ ከአለም

ኢትዮጵያዊው ሠዓሊ በአሜሪካ፤ ጃክሰን ጐዳና

ታዋቂዎች ጐራ እየተሰለፍኩ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ሥዕሌን ያዩና ይገረማሉ፡፡ አንድ ሰው ተሰጥኦው ኖሮት ትምህርት ካገዛው ምንም የማይሰራው ነገር የለም፤ ብዙ መስራት ይችላል፡፡ ከልጅነቴ ጀምሮ አጠገቤ ብዙ ሰዎች ስለነበሩ እየኮተኮቱ፣ ስራዬንና እኔን እያበረታቱ ነው ያሳደጉኝ፡፡ “አጥና” ስባል ወረቀትና እርሳስ ይዤ መሳል እጀምራለሁ፡፡ ለእኔ ጥናት ማለት እንደዛ ነበር፡፡

መቼ ነው መሳል የጀመርከው?ሶስተኛ ክፍል እያለሁ ለተማሪዎች ሥዕል

እሰራላቸው ነበር፡፡ አምስተኛ ክፍል ሳይንስ አስተማሪዬ በሥዕል ችሎታዬ ታደንቀኝ ነበር፡፡ ስድስተኛ ክፍል ስገባ፤ ዳይሬክተሩ ቀለም ይዞልኝ በትምህርት ቤቱ ውስጥ የተለያዩ የማስተማርያ ሥዕሎችን እስል ነበር፡፡ የልብ፣ የሳንባ፣ የኩላሊትና ሌሎች የሰውነት አካላት፡፡ ሰባተኛ ክፍል በፖለቲካ አስተማሪዬ አማካኝነት ሰሌዳ ላይ የሚለጠፉት ሥዕሎች ሁሉ የኔ ነበሩ፡፡ በቃ በትምህርት ቤት

እየታወቅሁኝ መጣሁ፡፡ ለቤተሰብ ተደውሎ ቀለምና ከለሮች እንዲገዛልኝ ተነገረልኝ፡፡ ዘጠነኛ ክፍል ስደርስ ሥዕል እየሰራሁ ገንዘብ ማግኘት ጀመርኩ፡፡

ለመጀመሪያ ጊዜ በሰራኸው ሥዕል ምን ያህል ገንዘብ እንዳገኘህ ታስታውሳለህ?

የሰው ፎቶግራፍ ስዬ ሃያ ብር ነበር ያገኘሁት። ሥዕል ጥርሴን የነቀልኩበት ሙያ ነው፡፡ ሠዓሊ ከሆንሽ ሌላ ነገር መሆን አትችይም፡፡ ትምህርት ስጨርስ አዲስ አበባ እህቴ ጋ መጣሁና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነጥበብ ት/ቤት ለአምስት ዓመት የሥዕል ትምህርት ተማርኩ፤ ማታ ማታ፡፡

ከትምህርት በኋላስ ምን ሰራህ?ሠዓሊ ተፈሪ ከሚባል ጓደኛዬ ጋር “ኤርታሌ”

የሚባል የሥዕል ስቱዲዮ ነበረን፡፡ በ90ዎቹ መጀመሪያ ይታተሙ ለነበሩ ጋዜጦችና መጽሔቶች:- እነ ጦቢያ፣ ኢትዮጵ፣ ምኒልክ፣ አስኳል፣ ጐህ፣ መብረቅ፣ ሙዳይ፣ ጥንቅሽ፣ ጽጌረዳ፣ ቃልኪዳን…የመሳሰሉ ህትመቶች የስማቸውን ዲዛይን እኔ ነኝ

የሰራሁላቸው፡፡ የርዕሰ አንቀፆችን ጽንሰ ሃሳብ ተቀብዬ ካርቱኖችንም እሰራ ነበር፡፡ ቦሌ ማተሚያ ድርጅትም ሰርቻለሁ፡፡

በአሊያንስ እንዲሁም፣ በሩሲያ የባህል ተቋም በተለያየ ወቅት ኤግዚቢሽን አቅርቤያለሁ፡፡ ሎሬት ጥበበ የማነህ ብርሃን፣ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ፣ እንዳልካቸው ተስፋ ገብረስላሴና ኃይሌ ገብረስላሴ ስራዎቼን ያደንቁልኝ ነበር። አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ከ10 በላይ ሥዕሎችን ገዝቶኛል፡፡ እንደውም ኃይሌ ምን እንዳለ ታውቂያለሽ? “አቅሙ ስለሌለኝ ነው እንጂ ብችል የአፍሪካ ሎሬት እለው ነበረ” ብሏል፡፡ ከእንግሊዝ የመጡ ጋዜጠኞች ፈረንሳይ ውስጥ ላለ መገናኛ ብዙሃን ቃለ መጠይቅ አድርገውኛል፡፡ ኤንቢሲ፣ ታይምስ፣ ቪኦኤ፣ ዶቼቬሌ፣ ኢትዮሚዲያ፣ ኢትዮጵያን ሪቪው…የዘገባ ሽፋን ሰጥተውኛል፡፡

እዚህ አገር ስንት ዓመት ቆየህ?ስድስተኛ ዓመቴን ይዣለሁ፡፡ ኒውዮርክ፣

በርሊንግተን የሚገኘው ቬርሞንት ስቱዲዮ ሴንተር፣ በየዓመቱ ለ50 አገራት ስኮላርሺፕ ይሰጣል፡፡ ውድድሩ ቀላል አልነበረም፡፡ ቬርሞንት ስቱዲዮ ሴንተር ከሃምሳ አገራት አምስት መቶ ሠዓሊዎች ነው የሚጋብዙት፡፡ ከአምስት መቶ ሠዓሊዎች ጋር ለመፎካከር የግድ ችሎታ እና ብቃት ይጠይቃል። ሥዕሎቼን ልኬ ተወዳደርኩና አሸነፍኩ፤ ከዛም ስቱዲዮው ወጪዬን ሁሉ ሸፍኖ ኒውዮርክ አመጣኝ። በገባሁ በአራት ቀን ውስጥ አስራ ሁለት ሥዕሎች ሳልኩኝ፡፡ ከአገሬ ይዤ የመጣሁት ነበር የመሰላቸው፡፡ ማቴሪያሉን ቼክ አድርገው (ሥዕሉ የሚሰራበትን ጥሬ እቃ) በጣም ተገረሙ። የፋውንዴሽኑ ፕሬዚደንት (የሮክፌለር ታናሽ ወንድም ነው) ወዲያው ኤግዚቢሽን እንዳሳይ ፈቅዶልኝ፣ ሥዕሌን ከሰቀልኩ በኋላ እስከመጨረሻው ቀን ድረስ ሳይቀየር እንደ ነገ ልሸኝ እንደዛሬ ነው የተነሳው፡፡

ለአስራ አምስት ቀን ፒትስበርግና ሲሊቫኒያ ውስጥ ኤግዚቢሽን አቅርቤአለሁ፤ ለአለም አቀፍ ተመልካች፡፡ ቬርሞንት የዓለም ሠዓሊዎች መኖሪያ ከተማ ነው፡፡ ምን ተብሎ ይታሰባል መሰለሽ? “ሠዓሊዎች አንድ ቦታ ላይ ሲሰበሰቡ፤ አለምን የሚቀይር ትልቅ ሃሳብ ያመነጫሉ”፡፡ በነገርሽ ላይ ከእኔ በፊት አንድ አፍሪካዊ ብቻ ነው በዚህ ስፍራ ኤግዚቢሽን የማሳየት ዕድል ያገኘው፡፡ ከኢትዮጵያ ሠዓሊያን የመጀመሪያው እኔ ነኝ፡፡ በኤግዚቢሽኑ ላይ 21 ሥዕሎቼን የከተማው ከንቲባ ነበር የገዛኝ፡፡

ከኒውዮርክ ወደ ኒው ኦርሊንስ፣ ከሰሜን ተነስተህ ደቡብ ማለት ነው…እንዴት መጣህ?

አሜሪካ ከገባሁ ጊዜ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ሥዕሌ ላይ ነው የኖርኩት፡፡ በጣት የሚቆጠር ሰዓሊ ነው እንደዚህ አይነት እድል የሚያገኘው። ረዥም ሰዓት የማሳልፈው ሥዕሌ ላይ ነው፡፡ መጀመሪያ ከኒውዮርክ ፒተርስበርግ ነው የሄድኩት፣ ከፒተርስበርግ

ሠዓሊ ወደ ገፅ 23 ዞሯል

Page 21: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 21

አድራጐት ድርጅት መሥርታ ነበር፡፡ ስዕሎቼን በ2ሺህ 800 ብር ሸጨው ለበጐ አድራጐት ሥራው ውሏል፡፡ ከፃፍኳቸው መፃሕፍት አንዳንዶቹ ለቴአትር ጨዋታ ተጠንተው በመድረክ ሲቀርቡ በተገኘው ገንዘብ ሕዝብ ሲጠቀምበት ማየቴ የመንፈስ ደስታ ሰጥቶኛል፡፡ ለጃንሆይ 25ተኛ ኢዮቤልዩ በዓል፤በሥማቸው የተሰየመው ቴአትር ቤት ተመርቆ ሲከፈት የእኔ ቴአትር (ዳዊትና ኦርዮን) ተመርጦ በመቅረቡ ላቅ ያለ የመንፈስ ከፍታ ተሰምቶኛል፡፡

መጽሐፍ ከመድረስ፣ ሥዕል ከመሳል፣ የቴአትር ጽሑፎችን ከማዘጋጀቴም ባሻገር ለፎቶግራፍ ጥበብ ልዩ ፍቅርና አክብሮት አለኝ፡፡ በ “የሕልም ሩጫ” መጽሐፌ ውስጥ በርካታ ፎቶግራፎችን ያስገባሁት በዚህ ምክንያት ነው፡፡ ፎቶግራፍ ለአገርና ለሕዝብ ታላላቅ ተግባራትን አከናውነው ያለፉ ባለታሪኮችን ምስል የሚያኖርልን ሙያና ጥበብ ስለሆነ ሌሎች ሰዎችም ፎቶግራፎችን እንዲያስቀምጡ አደራ እላለሁ፡፡

ሕፃን ከእናቱ ማህፀን በኩል ወደዚህ ዓለም ላይ የሚመጣው ለመልካም ወይም ለክፉ መልዕክት እንደሆነ የታወቀ በመሆኑ፤ ፓስካል (Pascal) የሚባል የፈረንሳይ ሊቅ አንድ ሕፃን አልጋው ላይ ተኝቶ ሲንፈራገጥ ባየ ጊዜ፣ ባርኔጣውን አውልቆ

ሩጫ ከገፅ18 የዞረ

ልብ ከገፅ 7 የዞረ

ስደት ከገፅ 11 የዞረ

“አንተ ሕፃን ለእንዴት ያለ ሥራ ተልከህ መጥተህ ይሆን?” ብሎ እጅ ነስቶት ያልፍ ነበር ይባላል፡፡

በምድር ሕይወት እንደምንመለከተው ራሱን በመጥላት፣ ወንድሙን በመውደድ፤ ገንዘቡንም ሕይወቱንም ለሀገሩ መስዋዕት በማድረግ የምግባር አርበኛ የሚሆን አለ፡፡ ሕዝብን በሰላም በመምራት በሕዝብ ልብ ውስጥ የሚነግስ የአገር መሪ ይኖራል፡፡ ጥቅሙን ሁሉ ለራሱ ሰብስቦ ወንድሙ የእሱ ለማኝ እንዲሆን የሚመኝና በዚህ ክፉ ሥራው የሚደሰትም አለ፡፡ ለዓለምና ለሰው ልጆች ጠቃሚ የሆኑ የጥበብ ሥራዎችን የሚፈለስፉ ምሁራን አሉ፡፡ የሰው ልጅ በዚህ መልኩ ለልዩ ልዩ ዓይነት ተግባር የተፈጠረ መሆኑ ይታያል፡፡

የሰው ልጅ ከመቃብሩ አፈር በላይ የሚቀር ታሪካዊ ሥራ ሳይሰራ መቶ ዓመት ቢቀመጥ ትርፉ ምንድነው? ሰው ከዕድሉ ጋር እስኪናገኝ ግን በከንቱ መድከም አይኖርበትም፡፡ ጥረትና ድካም ከዕድል ጋር ሲገናኙ ምን እንደሚመስሉ “የሕልም ሩጫ” ብዬ በሰየምኩት መጽሐፍ ባሰፈርኩት ጽሑፍና በአንድነት ካቀረብኳቸው ፎቶግራፎች፣ ከእኔ ሕይወትና ሥራ መማር ይቻላል፡፡

* * *የቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው የሕይወትና

የሥራ ታሪክን የያዘው “የሕልም ሩጫ” መጽሐፍ

በሁለት ሦስተኛ ገፆቹ የሰበሰባቸው ፎቶግራፎችም መረጃ ሰጪ ብቻ ሳይሆኑ ታሪክም ይናገራሉ፡፡ የአፄ ቴዎድሮስ፣ ዮሐንስ፣ ምኒልክ፣ የንግሥት ዘውዲቱና የእቴጌ ጣይቱ ምስሎችን ይዟል፡፡

የመጽሐፉ ባለታሪክ በልጅነታቸው በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲስ ከነበሩትበት ዘመን አንስቶ በወጣትነት፣ በአርበኛነት፣ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎችና ከኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ዲግሪያቸውን በተቀበሉበት ወቅት የተነሱትን ፎቶግራፎችንም አቅርቧል፡፡ አፄ ኃይለሥላሴ በአልጋ ወራሽነት የስልጣን ዘመናቸው ከፈረንሳይ መንግስት የተሰጣቸው የ”ቪላ ካሚስትራ” ሕንፃ፤ አልጋ ወራሹ አውሮፓን ዞረው በጐበኙባቸው ወቅት የነበረው ሁኔታ ምን እንደሚመስል ታሪክ የሚናገሩ ብዙ ፎቶዎችም አሉት፡፡

የባለታሪኩ ባለቤት ልዕልት የሻሽወርቅ ይልማ ላቋቋሙት የሕፃናት በጐ አድራጐት ድርጅት መርጃ ከሆኑትና 2ሺህ 800ብር ከተሸጡት ስዕሎች የተወሰኑት ፎቶግራፍ ተነስተው የመጽሐፉ አካል ሆነዋል፡፡ በዘይት ቀለም ቅብ ከሳሏቸው መካከል የኢየሱስ ክርስቶስ ምስል፣ የጐንደር ግንብ፣ የምጽዋ ድልድይ…ስዕሎች ይገኙበታል፡፡ በ1930 ዓ.ም በኢየሩሳሌም የሳሉትና እግዚአብሔር አንዱን ዘመን እያጠፋ ሌላውን ሲያበራ የሚያሳየው ስዕል በተለየ ሁኔታ ያስደምማል፡፡

ረጲ አካባቢ ይገኝ በነበረው መኖሪያ ቤታቸው ግቢ “የዓለም መታሰቢያ” የሚል ሐውልት ያሰሩት ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው፤ መጽሐፋቸው ሊያስተላልፉ የፈለጉትን መልዕክት ቀደም ብለው በሐውልቱ ላይ ያመለከቱ ይመስላል፡፡ በሐውልቱ አንድ ሽማግሌ ዓለምን ተሸክሞ ይታያል፡፡

ዓለምን በሚወክለው የድንጋይ ሉል ላይ “ኃጢአት ሸክምሽ የከበደ፤ ሌቦችና ቀማኞች የሚካፈሉሽ ዓለም ሆይ!” የሚል ጥቅስ ተጽፏል፡፡ በመኖሪያ ቤታቸው አፄ ኃይለሥላሴን ጨምሮ የዩጐዝላቪያ መሪ የነበሩት ፕሬዘዳንት ቲቶን መሰል ታላላቅ ሰዎችን ያስተናግዱ እንደነበር የሚያሳዩ ፎቶግራፎችም አሉ፡፡

“ላንድ ሕዝብ ነፃነት ማግኘት ብቻ የሚበቃ ነገር አይደለም፡፡ ነገር ግን ተቀባዩ ሕዝብ የነፃነትን ትርጉም ምን እንደሆነ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡

ቮልቴር የሚባል የፈረንሳይ ሊቅ “ነፃነት ለሰው ሁሉ የሚገባው መብቱ ሲሆን የወገኑን ኑሮ ሳያበላሽና መብቱን ሳያስደፍር በጥንቃቄ እንዲሰራበት ያስፈልጋል’ ይላል፡፡” በማለት በአንድ ወቅት በቤተመንግሥት ተገኝተው ንግግር የደረጉት ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው፤ ከንባብ፣ ከትምህርትና ከሥራ ልምድ ያገኙትን ዕውቀት በተለያዩ መፃሕፍት እያዘጋጁ በማሳተም ይታወቁ ነበር፡፡

አይነት “መች ተዋጋና ገና ነው ገና…” ማለት የሚቃጣቸው ግለሰቦችና ተቋማት ሲበዙበት “መሽናት ክልክል ነው” ከሚል ይልቅ “ትሸናና ትሸነሸናነህ!” የሚሉ ሚጢጢ ጉልበተኞች እየበዙ ሲሄዱ፣ መመሪያዎች፣ ዘጋቢ ፕሮግራሞች ምናምን… “ፈቀድን!” ከሚለው ይልቅ “ከለከልን!” ወደሚለው ትርጉም ሲያዘነብሉ…ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

ስንትና ስንት የሚያኮሩ ልምዶችና እሴቶች እንደ ሌሉት ሁሉ… “ከእከሌ የወሰድነው…” “ከእነ እከሌ የቀዳነው…” እየተባለ የ‘ፈረንጅ ፍርፋሪ’ ለቃሚ ሲያስመስሉት…ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

በ‘አፈ ቅቤውም’ በ‘አፈ ኮምጣጤውም’ የዘለፋ ናዳ የሚወርድባቸው የቀድሞ ዘመን ነገሥታት… አለ አይደል… “ሁሉንም ነገር አደረግናላችሁ፣ አፈራችንን ግን ይዛችሁ አትሄዱም…” አይነት ነገር እያሉ ጫማ እያሳጠቡ መርከብ ላይ እዳላሳፈሩ ሁሉ…ዛሬ በየቦታው ‘ቅድሚያ ለነጭ’ አይነት ነገር እየበዛበት፣ ጭርሱን “ለፈረንጅ ጫማውን ብታብጥለትስ ምን አለበት…” ሊባል ምንም ያልቀረን ሲመስል…ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

አንዳንድ ቦታ በችሎታ ሳይሆን በመጠሪያ ስሙ ብቻ ማንነት ‘እየተበጀለት’ ብቁ ለሆነበት ቦታ ሁሉ “ብቁ አይደለህም…” ሲባል፣ በሠለጠነበትና የሥራ ልምድ ባካበተበት ቦታ ሳይሆን…አለ አይደል… በተወለደበት ስፍራ ሲመዘን… ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” እያለ ነው፡፡

ስሙኝማ…እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ…የስም ነገር የምር አስቸጋሪ ነው። ምን መሰላችሁ…አንዳንድ እዚቹ አገር በሚገኙ ስፍራዎች አገልግሎት ለማግኘት ስም እስከ አያት ድረስ ይጠየቃል የሚባል ነገር አለ፡፡ መቼም ጉዳችን ተወርቶ አያልቅ!

እግረ መንገዴን የሆነ ነገር ትዝ አለኝ… አንድ ጊዜ አንድ በ‘ተጨማሪ ሰዓት’ ሊንቀሳቀስ እየተቃረበ የነበረ ወዳጄ የሆነች እንትናዬ ላይ…በትኩሶቹ ቋንቋ… ‘ጆፌ ጥሎ’ ሲያንዣብብ ይከርምና ሊሳካለት ጫፍ ይደርሳል፡፡ ታዲያላችሁ…ይሄን ሁሉ ጊዜ የሚያውቀው ዋናውን ስሟን ሳይሆን ‘ባክአፕ’ መጠሪያዋን ነው፡፡

ታዲያላችሁ…አንድ ቀን እውነተኛ ስሟ ከሦስተኛ ወገን ይነገረዋል፡፡ መጥቶ ምን ቢለኝ ጥሩ ነው…“አንተ ያቺ እንትና ስሟ እንትና ነው እንዴ!” አለላችሁና…በቃ የፕሮጀክት ትግበራውን አቆመዋ! እዚህ ደረጃ መድረሳችን በጣም አያሳዝንም!

ሰዋችን ዝም ብሎ እያየ ያለ ድምጽ “ልብ አድርጉልኝ!” የሚያስብሉት ነገሮች የሚቀንሱበትን ዘመን አንድዬ ያምጣልንማ!

ደህና ሰንብቱልኝማ!

ችግር የተነሳ፣ ሴት ሴቶቹን ገና በአስራ ሁለትና አስራ ሶስት አመት እድሜያቸው ከት/ቤት ጎትተው አውጥተው ይድሯቸዋል፡፡ ይህንን የሚያደርጉት ከልጆቹ ይልቅ ለራሳቸው እያሰቡ ነው፡፡ ትላልቅ ልጆች በኑሮ እሳት እየተቃጠሉ በሚልኩት ገንዘብ ከስር ከስር እየወለዱ ያሳድጋሉ፡፡ በዚህ መሃል ወላጆች ራሳቸውን ከሃላፊነት ገለል ያደርጋሉ፡፡ ጎበዝ ባህላችን መፈተሽ አለበት!

ብዙ ወላጆች እንደ ወላጅ ከሚጠበቅባቸው ሃላፊነቶች ውስጥ ሩቡን እንኳን ሳያሟሉ ነው “እናት” እና “አባት” ተብለው የሚጠሩት። ልጅን በቂና የተመጣጠነ ምግብ ሳያበሉ፣ በቂ የጨዋታና የመዝናኛ እንዲሁም የዕረፍት እድል ሳይሰጡ፣ ንፅህናና ጤና ሳይጠብቁ፣ የትምህርት መሳሪያ አሟልተው ሳያስተምሩ እንዲሁ በጭፍን ወልደው፣ በጭፍን ነው የሚያሳድጉት፡፡ (የማሳደግ ከተባለ) ሰዎች ለመውለድ ከመወሰናቸው በፊት ያለባቸውን ሃላፊነት ልክ የሚያሳይ ዝርዝር የሚፈርሙ ቢሆን ኖሮ እንዴት ጥሩ ነበር፡፡

በዓለም ላይ እንደ ኢትዮጵያ ህፃናትና ወጣቶች አድገው ሳይጨርሱ ወላጆቻቸውን ለመጦር የሚተጉ (የሚያልሙ) ዜጎች መኖራቸውን እጠራጠራለሁ፡፡ ከፍ ብለው ወደ ስደት ከሚያቀኑት ሌላ በመኖሪያ አካባቢያቸው ጎዳና ላይ ሰርተው ወላጆቻቸውን ለመደገፍ የሚተጉ ብዙ ሺህ ኢትዮጵያውያን ህፃናት አሉ፡፡ ወላጆቻቸውም ቢሆኑ እነዚህን ልጆች ለመሸጥ፣ ለማከራየት (በቤት ሰራተኝነት በሞግዚትነት፣ በገበሬነት፣ ወዘተ ከማሰማራት) ወደ ኋላ አይሉም፡፡

በርካታ ወላጆች የልጃቸውን ህይወት አስይዘው (መድበው ልበል በቁማርተኞች ቋንቋ) ቁማር ይጫወታሉ፡፡ አንድ ቁማርተኛ ቁማር የሚጫወተው ትርፍ ለማግኘት (ለመብላት) ቢሆንም ሊከስር (ሊበላ) እንደሚችልም ያውቃል፡፡ ቁማርተኛ ወላጆችም ልጆቻቸውን (አስይዘው/መድበው

ሲቆምሩ) ወይም ወደ አረብ አገር ሲልኩ ልጆቻቸው ሊሞቱ እንደሚችሉ ያውቃሉ፡፡ ሆኖም የሚጠፋው የነሱ ሳይሆን የምስኪን ልጆቻቸው ህይወት መሆኑን ስለሚያውቁ “ልጄ ይሞትብኛል” ብለው ከመስጋት ይልቅ ልጄ በረሃውን አቋርጦ፣ከውሃ ጥም፣ ከጊንጥ ወዘተ ተርፎ ገንዘብ ይልክልኛል ብለው ያስባሉ። ቁማርተኛ ለምሳሌ ካርታ ተጫዋች የአሁኑን ባሸንፍ (ብዘጋ)፣ ከዚያ ደግሞ የሚቀጥሉትን ሁለት ጨዋታዎችም በተከታታይ ባሸንፍ ብሬን ላስመልስ እችላለሁ ወይም ብዙ ብር ልበላ እችላለሁ ብሎ ተስፋ እያደረገ እንደሚጫወተው ሁሉ፣ ጨካኝ ወላጆችም ልጆቻቸው ቁጥር ስፍር በሌለው አደጋ ውስጥ አልፈው የገንዘብ ምንጭእንዲሆኑላቸው ተስፋ ያደርጋሉ (ይቆምራሉ)፡፡

በነገራችን ላይ ሴት ልጆቻቸውን በህፃንነታቸው የሚድሩ ወላጆችም ያው ቁማርተኞች ናቸው፡፡ ሴት ልጅን ያለ እድሜዋ መዳር ያለውን ጣጣ በከፊል ያውቁታል፡፡ ለምሳሌ ለፊስቱላ፣ ለማህፀን ካንሰር፣ ለኤችአይቪ ኤድስ ወዘተ መጋለጥ አለ፤ በምጥ መሞትም አለ፡፡ ራስ ወዳድ ወላጆች ግን የሚያስቡት የራሳቸውን ጥቅም ብቻ በመሆኑ “በልጅ አመካኝቶ ይበላል አንጉቶ” እንዲሉ ከወግና ባህል ጀርባ ተደብቀው ለልጆቻቸው ያሰቡ በመምሰል ነው ልጆቻቸውን የሚድሩት፡፡

በነገራችን ላይ የልጅ ጉልበት ላይ ጥገኛ መሆን፣በልጅ የመደገፍ አባዜ በብዙ ወላጆች ላይ ይታያል፡፡ ልጆችን መላክ፣ ማዘዝ፣ ስርዓትና ስራ ለማስተማር የሚረዳ መሆኑ ባይካድም ወላጆች የምንፈፅመው ግን ከዚያ አልፎ “የጉልበት ብዝበዛ” በሚያሰኝ ደረጃ ነው፡፡ እስቲ እንትን አምጣልኝ፣እንትን አቀብለኝ፣እንትን እጠብልኝ…ማለቂያ የሌለው ትእዛዝ! ለምን? ይህ በጥሩ ባህል ወይም ልማድነት “ተመዝግቦ” የምናገኘው ኢትዮጵያዊ የወላጅና ልጅ ግንኙነት (መስተጋብር) ሲመቸው ወደ ከፋ ብዝበዛ ማምራቱ ይስተዋል ካልኩ ይበቃል፡፡

ግብዓቶች ናቸው፡፡ ሲሚንቶ፣ ብረት፣ የመሳሰሉት እጥረትና ጥራት እንዲሁም ዋጋ ሲሆን ሌላው ችግር የሰለጠነው የሰው ሀይል አንድ ቦታ ተቀጥሮ አለመስራት ነው፡፡ በአንድ ቦታ ረግተው አይቆዩም።

ስራ ከጀመራችሁ አንስቶ ስንት ቤቶች ለደንበኞች አስረክባችኋል? በአመት ስንት ለማስረከብስ አቅዳችኋል?

እስካሁን ብዙ ቤት ለደንበኞች አስረክበናል። ገብተው መኖር የጀመሩ ብዙ ናቸው፡፡ እንዲሁ ተረክበው መንገድ እስኪስተካከል ብለው የቆዩ ደንበኞችም አሉን፡፡ በየአመቱ ከ40-50 ቤቶች እናስረክባለን፡፡ ህዳር መጨረሻ ላይም ከአርባ የሚበልጡ ቤቶች ለደንበኞች እናስረክባለን፡፡

የወደፊት እቅዳችሁ ምንድነው?ወደፊት ለህብረተሰቡ አቅሙን ያማከለ

አፓርትመንት ሰርተን ለማስረከብ እቅድ አለን። በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እየታገዝን እስከ ዛሬ ከሰራናቸው ትምህርት ወስደን የተሻሉ ቤቶችን እንገነባለን ብለን እናስባለን፡፡

መኖሪያ ከገፅ 12 የዞረ

ያዝረከረኩትን ሰብሰብ ላድርግ፡፡ ልጆቻቸውን ለስደትና ለመዘዙ የሚያጋልጡት ራስ ወዳድ ወላጆች ናቸው፡፡ ደላሎች በሚፈፅሙት የህግ ጥሰት ይጠየቁ። ወላጆችም ልጆቻቸው ላይ የሚያደርሱትን ጫና እንዲቀንሱ፣ከልጆቻቸው ትከሻ ላይ እንዲወርዱ ይመከሩ፣ ይወቀሱ፡፡ ወላጆች በልጆቻቸው ገንዘብ እርስ በርስ መፎካከራቸውን ያቁሙ፤ ይፈሩ። በልጅ ገንዘብ የከበሩ፤በልጅ የድጎማ ገንዘብ ያለፈላቸው ወላጆች፤ በሰፈርተኛው መሞገሳቸው ይቁም፡፡ ወላጆች ህፃናት ልጆቻቸው አረብ አገር እንዳይሄዱባቸው ሰልፍ ይውጡ፣ ይፈራረሙ፡፡ በዚህ አስተሳሰብ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ካልተፈጠረ ልጆች “ወላጆቻቸውን” ለመርዳት ሲሉ ከዚህም የከፋ ችግር ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፡፡

ጥሩ ወላጆች ያደረጉትን ነገር ልንገራችሁና ፅሁፌን ልቋጭ፡፡ እናትና አባት እዚሁ አገራችን ውስጥ ልጃቸውን በተገቢው መንገድ አሳድገውና አስተምረው ለጥሩ ደረጃ ያደርሳሉ፡፡ ልጃቸውም ጥሩ ትምህርት የቀመሰች ነበረችና ውጪ አገር ስራ አግኝታ መኖር ትጀምራለች፡፡ ከዚያም እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ልጅ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ለእናትና አባቷ የኑሮ መደጎሚያ ገንዘብ ትልክላቸው ጀመር። ወራት አለፉ፣ አመታትም ተከተሉ፡፡ ልጂት በሆነ ጊዜ ወላጆችዋን ለማየት ወደ አዲስ አበባ መጣች፡፡ እናትና አባቷ እጅግ አስደናቂ ነገር አድርገው ቆዩዋት። ድል ያለ ድግስ እንዳይመስላችሁ፡፡ ልጃቸው በላከችላቸው ብር ጥሩ ቤት ገዝተውላት ኖሮ እንዲህ አሏት፡፡ “ይህ ያንቺ ቤት ነው፤ የገዛንልሽም በብርሽ ነው፡፡ እኛ ያለን የጡረታ ገንዘብ ይበቃናል፡፡ ውጪ አገር መኖርና መስራት በበቃሽ ጊዜ ትኖሪበታለሽ ብለን ነው የገዛንልሽ” ልጅት ወላጆቿ ማስተማርና ከፍ ያለ ደረጃ እንድትደርስ ማድረጋቸው አንሶ ለቀጣይ ዘመንዋ የሚበጃትን ስጦታ ስላበረከቱላት የደስታ እንባ አንፎለፎች፡፡ አቅፋ ሳመቻቸው፡፡ ተሳሳቁ፡፡ እንዲህም አለ ለማለት ያህል ነው፡፡

Page 22: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 22 ዓለምአቀፍ

አልአዛር ኬ

መልሱን በገፅ 24 ይመልከቱ

ሐሳብዎን ይግለፁ!የእርስዎ ድምፅ!

እስቲ ገምቱ!

አዲሱ ፕሬዚዳንት፣ የተቃውሞ ሰልፍና መብራት

1. ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ባለፈው ሳምንት አርብ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ተቃዋሚዎች ከጥቂት ወራት ወዲህ አጠናክረው የቀጠሉትን የተቃውሞ ሰልፍ በተመለከተ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ፤ ተቃዋሚዎች የሚያነሱት ጥያቄ ተደጋጋሚና ፋይዳቢስ መሆኑን ጠቁመው፣ እያንዳንዱ ፓርቲ በየቀኑ ለሚያደርገው ሰልፍ ጥበቃ መመደብ ስለማይቻል የተቃውሞ ሰልፉ ላይቀጥል ይችላል ብለዋል፡፡ ከዚህ የጠ/ሚኒስትሩ ንግግር በመነሳትም አንዳንድ ወገኖች ተቃውሞ ሰልፍ የማድረግ ህገመንግስታዊ መብት ዳግም ሊታገድ እንደሚችል ስጋት አላቸው፡፡ እርስዎስ ይሄን ስጋት ይጋሩታል?

A) እንዴታ፤ ሰልፍማ አከተመ!B) አልጋራውም፤ ህገመንግስታዊ መብት እኮ

ነው!C) መንግስት ላይዘልቅበት ማን ጀምር አለው?!D) ታገደ አልታገደ ለውጥ የለውም

2. አገሪቷን ለ12 ዓመታት በፕሬዚዳንትነት ያገለገሉት አቶ ግርማ ወልደጊዮርጊስ በሥልጣን ዘመናቸው ውጤታማ እንዳልነበሩ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ባለፈው ሰኞ በፓርላማ ከተሾሙት አዲሱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ከቀድሞው የተለየ አዲስ ነገር ይጠብቃሉ?

A) አልጠብቅም፤ ፕሬዚዳንት ተሾመ እንጂ ህገመንግስቱ ተሻሻለ እንዴ?

B) እጠብቃለሁ፤ ትንሽም ብትሆን አዲስ ነገር ይመጣል

C) ጉልቻ ቢለዋወጥ ወጥ አያጣፍጥም!D) ከፀሃይ በታች ምንም አዲስ ነገር የለም

3. ባለፈው ዓመት በፓርላማ የታየው አዲስ የመነቃቃት ስሜት ዘንድሮም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ብዙዎች ተስፋ አድርገዋል፡፡ እርስዎስ ምን ይላሉ?

A) ወደፊት መራመዱ ቢቀር ወደ ኋላ አንመለስም B) የነብርን ዥራት አይዙም፤ ከያዙም አይለቁም C) ዲሞክራሲ የህልውና ጉዳይ ነው ተብሎ የለ! D) ጨው ለራስህ ስትል ጣፍጥ…

4. አዲሱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ በፓርላማ ሹመታቸው መጽደቁን ተከትሎ ባደረጉት ንግግር፤ የኤሌክትሪክ ሃይል አገልግሎት ላይ ለሚታየው ችግር መሰረታዊው መንስኤ፣ ኤሌክትሪክ የማመንጨትና የማሰራጨት ስራዎች በአንድ ድርጅት እንዲካሄዱ መደረጋቸው እንደሆነ ጠቅሰው፣ ችግሩን ለማስወገድ የመብራት ሃይል ኮርፖሬሽን ለሁለት ተከፍሎ እንደ አዲስ እንደሚዋቀር ገልፀዋል፡፡ ብዙዎች እርምጃው ለሃይል መቆራረጡ መፍትሔ ይሆናል በሚለው ላይ ጥርጣሬ አላቸው፡፡ እርስዎስ?

A. በጨለማ አውሎ እያሳደረኝ እንዴት አልጠራጠር!

B. በጥናት ላይ የተመሰረተ መፍትሄ ከሆነ አልጠራጠረውም

C. መንግሥት እስከዛሬ የት ሄዶ ነው?D. ተስፋም ጥርጣሬም የለኝም!

5. ላለፉት ሁለት ዓመታት አዲስ አበባን ሰንጐ የያዛት የትራንስፖርት ችግር፣ ነዋሪዎችን ጠዋት ማታ በወረፋና በግፊያ እያንገላታ ቢሆንም እስካሁን መፍትሔ የሚዘይድ አንድም የመንግስት አካል ብቅ አላለም፡፡ ችግሩ መቼ ይፈታል ብለው ያስባሉ?

A) ምናልባት የባቡር ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ B) የታክሲ የቀጣና (ታፔላ) አሰራር ሲቀር C) ዘርፉ ለግል ባለሃብቱ አዋጪ ሲሆን D) ችግሩን የፈጠሩት ቢመልሱት ይሻላል

እነዚህን ጥያቄዎች በመመለስ የፈሊጣዊ አነጋገር ችሎታችሁን አዳብሩ፡፡

1. ሀብተ ስጋ2. ሀብተ ሰባራ3. ሀብተ ነፍስ4. ህግ ገባ5. ሆድ አይበልጠውም6. አልሚና ለሚ7. ዋንጫ ልቅለቃ8. ለብሰሽ ፍጅው9. ላባ ቀረሽ10. ልቡ ሰባ

ከጥቂት ሳምንታት በፊት በዚሁ ጋዜጣ “ፔን” በተባለ ከደራሲያን ጋር በሚሰራ ድርጅት ጋባዥነት አይስላንድ የተባለችውን አውሮፓዊት ሀገር ጐብኝቶ

የመጣ አንድ ወዳጃችን በዋና ከተማዋ ሬይካቪክ በቆየባቸው ቀናት ከተመለከታቸው ነገሮች ውስጥ ይበልጥ ትኩረቱን የሳቡትን ለይቶ በመፃፍ አስነብቦን ነበር፡፡

በአይሁዶች ሚሽናህ “ካለው ላይ የጨመረ እርሱ የአባቱን ምርቃት፣ የእናቱንም እቅፋት ያገኛል” የሚል የቅድስና ቃል ተጽፎ ይገኛል፡፡ ይህ የዛሬው የእኔ ጽሑፍም አይስላንድ ስለተባለችውና በለምአቀፉ ሚዲያ በክፉም ሆነ በበጐ አዘውትሮ ስሟ ሲነሳ ስለማንሠማት አውሮፓዊት ሀገር በርካታ ነገረ ስራዎች ውስጥ የእኔን ትኩረት ይበልጥ የሳቡትን ጉዳዮች በማንሳት ከሳምንታት በፊት ወዳጃችን ከሰጠን ላይ ለመጨመር ነው፡፡ አይስላንድ ከአለማችን ሰሜናዊ ጫፍ በቅርብ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ ይህ ቅርበቷ በቅዝቃዜና በበረዶ የተሞላች ሀገር እንድትሆን አድርጓታል፡፡

ይህ በረዶና ቅዝቃዜዋ እነሆ የስሟ መጠሪያ ለመሆንም በቅቷል፡፡ እንዲህ ያለው የአይስላንድ መልክአምድራዊ አፈጣጠሯ አብዛኛውን ጊዜ በደንብ ለማያውቋት ወይም ላይ ላዩን ብቻ የሚያውቋት ሰዎች ልክ ወዳጃችን ባለፈው ጊዜ ጽፎ እንዳስነበበን ዋነኛ ትኩረታቸውን በአየር ንብረቷና ከአየር ንብረቷ ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ እንዲያደርጉ ዋነኛ ምክንያት ሆኖአቸዋል፡፡

ይህ ግን አሳሳች ነገር ነው፡፡ በርካቶች አይስላንድን በአንድ ጐን ወይም በአንድ አቅጣጫ ብቻ እንዲያዩዋት አድርጓቸዋል፡፡ የምዕራብ አፍሪካ ነዋሪዎች “ከሁሉም ምርጥ የሆነው ዛፍ ጭው ካለው ገደል አፋፍ ላይ ይበቅላል፡፡” የሚል አባባል አላቸው፡፡ ይህ አባባል አይስላንድን ምናልባት ከሌላው በተሻለ ሊገልፃት ይችላል፡፡

እንደ እውነቱ ከሆነ አይስላንድ ጥልቅ ከሆነው ገደል አፋፍ ላይ የበቀለች ምርጥ ዛፍ ናት፡፡ በበርካታ ዘርፍ ያሉት ነገረ ስራዎቿ ይህንን እውነታ በሚገባ ማረጋገጥ ይችላሉ፡፡

አንድ መቶ ሶስት ሺ ስኩዌር ኪሎሜትር በሚሆነው ጠቅላላ መሬቷ ላይ ሶስት መቶ ሃያ አንድ ሺ ስምንት መቶ ሃምሳ ሰባት የሆነው ጠቅላላ ህዝቧ ሰፋ ሰፋ ብሎ በመስፈር ይኖራል፡፡ ይህም ዘርዛራ የህዝብ አሰፋፈር ካላቸው የአውሮፓ ሀገራት መካከል ቀዳሚ እንድትሆን አስችሏታል፡፡

የአይስላንድ ባህል ከሀገሪቱ የኖርስ ቅርስ የተወረሰ ነው፡፡ አብዛኛዎቹን አይስላንዳውያን ስለዘር ሀረጋቸው ብትጠይቋቸው ከኖስና ጋይሊክ (ሴልቲክና ሻይኪንግ) ሰፋሪዎች የመጡ ወይም የሚመዘዝ መሆኑን አስረግጠው ይነግሯችኋል፡፡

የማንነታቸውን ስረ መሠረት ጥንቅቅ አድርገው የሚያውቁት አይስላንዳውያን ደግሞ የመጀመያው የኖርስ ሰፋሪ ኢንጐልፈር አርናርሰን እንደሚሰኝና የሰፈራ ዛኒጋባውንም በስምንት መቶ ሰባ አራት አመተ ምህረት ዛሬ የአይስላንድ ዋና ከተማ በሆነችው በሬይካቪክ ቀልሶ መኖር እንጀመረ በሚገባ

አይስላንድ - የደራሲያንና የአንባብያን ሀገር

ያብራሩላችኋል፡፡ ይህንን ታሪክ የሚነግሯችሁ ደግሞ እንዲሁ በወሬ ብቻ ሳይሆን በቁፋሮ የተገኙ ታሪካዊ ማስረጃዎችን በማቅረብ ነው፡፡

የአየር ንብረት ተመራማሪዎች በቀደሙት የኖርስና ጋይሊክ (የሴልቲክና ቫይኪንግ) ሰፋሪዎች ጊዜ የአይስላንድ የአየር ንብረት አሁን ካለው እጅግ በተሻለ ሞቃት እንደነበረ፤ አሁን ያለው አንድ በመቶ የሚሆነው የሀገሪቱ የደን ሽፋን ያኔ ሃያ አምስት በመቶ እንደነበረ በማስረጃ አስደግፈው ይናገራሉ፡፡

አይስላንዳውያን በዘጠኝ መቶ ሰላሳ አመተ ምሕረት የአይስላንዲክ ኮመንዌልዝን እንዲቆጣጠር ያቋቋሙት የህግ አውጭና፣ የህግ አስፈፃሚ ምክር ቤት ወይም ፓርላማ ህልውናውን እንደጠበቀ እስከ አስራ ሶስተኛው ክፍለዘመን ድረስ መዝለቅ ችሎ ነበር፡፡

በስተርላንግ ዘመን የተፈጠረው የውስጥ ትግልና የእርስ በርስ ግጭት በ1262 ዓ.ም ዛሬ “የድሮው ስምምነት” እየተባለ ለሚጠራው ውል መፈረም ዋነኛ ምክንያት ሆነ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ይህ ውል ተራ ውል አልነበረም፡፡ ራሷን ችላ ትኖር የነበረችው አይስላንድ በኖርዌይ የዘውድ መንግስት ስር እየገበረች እንድታድር የሆነችው በዚህ ስምምነት አማካኝነት ነበር፡፡

ከዚህ ክስተት በሁዋላ የተከተሉት አመታት ለአይስላንድና ለህዝቦቿ መልካም አመታት አልነበሩም፡፡ የአየር ንብረቷ ቀስ በቀስ ግን ባልተቋረጠ ፍጥነት እየቀዘቀዘና እየከፋ ሄደ፡፡ በተከታታይ የደረሱበት የእሳተ-ገሞራ ፍንዳታዎች፣ከግግሩ በረዶ ጋር ተዳምሮ ቀላል የማይባል መጠን ያለውን መሬት ለእርሻ አገልግሎት እንዳይውል አደረገው፡፡ ሰፊ ይባል የነበረው የደን ሀብትም በከፍተኛ ፍጥነት እየተመናመነ ሄደ፡፡

ይህ ሁኔታ የአይስላንዳውያንን የእለት ተዕለት ህይወት እጅግ መራራና ሸክሙ የማይቻል ከባድ እዳ አደረገባቸው፡፡ በዚህ የተነሳም አይስላንዳውያንም ሆኑ ሀገራቸው ከአውሮፓ እጅግ ደሀ ከሆኑት ሀገራት ተርታ መሰለፍ ግድ ሆነባቸው፡፡

በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ በ1402 አ.ም እና በ1494 አ.ም የተከሰተውና “ጥቁሩ ሞት” እየተባለ የሚጠራው ወረርሽኝ እንዳይሞቱ እንዳይሸሩ አድርጎ ክፉኛ ደቆሳቸው፡፡ በተለይ በ1402 አ.ም የተከሰተውና ለሶስት አመት ያህል የዘለቀው የመጀመሪያው ወረርሽኝ ከጠቅላላው ህዝባቸው ከሀምሳ እስከ ስልሳ በመቶ የሚሆነውን በመፍጀት አይስላንዳውያንን ከምድረ ገፅ ነቅሎ ሊያጠፋው ክፉኛ ተገዳድሮአቸው ነበር፡፡

የናፖሊወንን ጦርነት ተከትሎ በ1814 አ.ም የተፈረመው የ“ኪየል ውል” የዴንማርክ - ኖርዌይ ግዛት ለሁለት እንዲከፈልና ራሳቸውን የቻሉ የንጉሱ ነገስት መንግስት እንዲሆኑ አደረጋቸው፡፡ በኖርዌይ አገዛዝ ስር የነበረችው አይስላንድም ዴንማርክን በአዲስ ገዢነት ተቀብላ ማደር ጀመረች፡፡

ከኖርዌይ ጋር ሲወዳደር ዴንማርክ አይስላንድን የገዛቻት ከብረት በጠነከረ ክንድ ነበር። ለአይስላንዳዊያን ግን ይህ በወቅቱ የቅድሚያ ትኩረት የሚሰጡት ጉዳያቸው አልነበረም፡፡ ምክንያቱም ደግሞ ከዴንማርክ የጭቆና አገዛዝ ይልቅ ከግራና ከቀኝ ጎናቸውን ሰቅዞ ይዞ አላፈናፍን ያላቸውና ህልውናቸውን በከፍተኛ ደረጃ እየተፈታተናቸው ያለ ትልቅ ጉዳይ ከፊትለፊታቸው ተደቅኖባቸው ነበርና ነው፡፡ ይህ ትልቅ አደጋ ሌላ ነገር ሳይሆን በየእለቱ ቅዝቃዜውና የበረዶው ግግር እየከፋ የመጣው የሀገራቸው የአየር ንብረት ጉዳይ ነበር፡፡እየከፋ የሄደው የአየር ንብረት በተለይ በአስራዘጠነኛው ክፍለዘመን መጀመሪያ አካባበቢ በርካታ አይስላንዳዊያን ወደ አዲሱ አለም በዋናነት ደግሞ ወደ ካናዳ ጨርቄን ማቄን ሳይሉ እንዲሰደዱ አድርጓቸዋል፡፡ ለምሳሌ በ1820 አ.ም ሰባ ሺ ከሚሆኑት አይስላንዳዊያን መካከል አስራ አምስት ሺ የሚሆኑት ወደ ማኒቶባ ካናዳ ተሰደዋል፡፡ ይህ ቁጥር በሌላ አነጋገር ሲገለጽ በወቅቱ ከነበረው የአይስላንድ ጠቅላላ የህዝብ ቁጥር ከሃያ በመቶ በላይ የሚሆነው ህዝብ በአንድ አመት ውስጥ ብቻ ሀገሩን ጥሎ ተሰዷል ማለት ነው፡፡

በ1943 አ.ም የሚያዚያ ወር መጨረሻ ላይ ለሀያ አምስት አመታት የዘለቀው የዴንማርክና አይስላንድ ህብረት ስምምነት ፈረሰ፡፡ በቀጣዩ አመት ግንቦት ሀያ ቀን ደግሞ አይስላንዳዊያን ከዴንማርክ አገዛዝ በመላቀቅ የራሳቸውን ነፃ ግዛት ለመመስረት ድምፃቸውን ሰጡ፡፡ ሰኔ አስራ ሰባት ቀን 1944አ.ም ላይ ደግሞ ነፃ የአይስላንድ ሪፐብሊክን በሟቋቋም ስቪን ቢዬንሰንን የመጀመሪያው ፕሬዚዳንታቸው አድርገው መረጡ፡፡

ይህ የአይስላንድ የቀድሞው ታሪኳ ነው፡፡ ከነፃነት በሁዋላ ያለው የአይስላንድ የኢኮኖሚ፣የፖለቲካ፣ማህበራዊና የአለም አቀፍ ግንኙነት ታሪኳበጣም አስገራሚ ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ይህቺ ድምጿም ሆነ ወሬዋ እምብዛም የማይሰማው አውሮፓዊት ሀገር በስነ ፅሁፍ ረገድ ያላት ታሪክና ለአለም ስለፅሁፍ እድገት ያበረከተችው አስተዋፅኦ እጅግ አስደናቂ ነው፡፡ እነዚህን የሳምንት ሰው ይበለንና ሳምንት እንመለስበታለን፡፡

ረብሻ ከገፅ 1 የዞረተዘግቶ ነበር፡፡

የረብሻው ምንጭ፣ ከሊቢያ ወደ ጣሊያን ሲጓዙ ለሞቱ በርካታ ኤርትራውያን የተዘጋጀ የመታሰቢያ ስነ ስርዓት እንደሆነ ምንጮቻችን ጠቅሰው ሻማ በማብራት የተጀመረው የመታሰቢያ ምሽት ወደ ተቃውሞ ረብሻ መቀየሩን አስታውሰዋል፡፡ በካምፑ ውስጥ የተፈጠረው ረብሻ ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል በሚል ውሳኔ የፀጥታ ሀይሎች ጣልቃ እንደገቡ ምንጮቹ ጠቅሰው፤ በረብሻውና በግጭቱ የአንድ ሰው ህይወት እንደጠፋ ተናግረዋል፡፡

የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ

ኮሚሽን (UNHCR) የህዝብ ግንኙነት ተወካይ አቶ ክሱት ገብረእግዚአብሔር፤ በሜዲትራኒያን ባህር ላምፑዱስ የተባለ ደሴት አቅራቢያ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች የሻማ ማብራት ስነ ስርአት እናደርጋለን በሚል የተጀመረው ፕሮግራም ለምን ወደ አመፅ እንዳመራ አናውቅም ብለዋል፡፡ ስደተኞቹ ወደ ጎንደር የሚወስደውን መንገድ እንደዘጉ አቶ ክሱት ጠቅሰው፣ የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እና አብረውን የሚሠሩ የሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ላይ ተቃውሞ ተቀስቅሶ የቢሮ መስኮቶችና በሮች ተሠባብረዋል ብለዋል፡፡ ካምፕ ውስጥ የነበሩና አማራጭ ያጡ

ወገኖች በሊቢያ በኩል ወደ ጣሊያን ለመግባት ሲሞክሩ ሞተዋል የሚል ሃሳብ በስደተኞች በኩል እንደተሰነዘረ አቶ ክሱት ጠቁመዋል፡፡

የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን፣ በህጋዊ መንገድ ስደተኞችን ቢያጓጉዝ ኖሮ የበርካቶች ህይወት አይጠፋም ነበር በማለት በኮሚሽኑ ቢሮዎች ላይ ጥቃት እንደተፈፀሙ ሰምተናል ብለዋል-አቶ ክሱት፡፡ ስደተኞች ወደተለያዩ አገራት የሚጓጓዙት በኮሚሽኑ ፍላጎት ሳይሆን በተቀባይ አገራት በጎ ፈቃድ ነው ያሉት አቶ ክሱት፤ ኮሚሽኑ ለስደተኞች እንግልት ተጠያቂ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡

የናፖሊወንን ጦርነት ተከትሎ በ1814 አ.ም የተፈረመው የ“ኪየል ውል” የዴንማርክ - ኖርዌይ ግዛት ለሁለት እንዲከፈልና ራሳቸውን የቻሉ የንጉሱ ነገስት መንግስት እንዲሆኑ አደረጋቸው።

በኖርዌይ አገዛዝ ስር የነበረችው አይስላንድም ዴንማርክን በአዲስ ገዢነት ተቀብላ ማደር ጀመረች፡፡

Page 23: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 23

ሠዓሊ ከገፅ 20 የዞረ

ቢዝነሱ ከገፅ 19 የዞረ

“በቃ ይኸው ነው”“ይሄን ሁሉ ስም ያወጣልህ ማነው?”“ግማሹን ጉዋደኞቼ፣ሌላውን ደግሞ የሰፈር

ሰው”“ለምን ነው እንዲህ አይነት ስም ያወጡልህ?” “በአንዳንድ ድርጊቴ…” “ለምሳሌ?”“አሞራው ያሉኝ ሞባይል ስለምሰራ ነው”“መስራት ማለት?”“ያው አንዳንድ ሰዎች ተዝናንተው በሞባይል

ሲያወሩ ፣ነጥቄያቸው ስለምሮጥ እ…‹አፍን› ያሉኝ ደሞ፣ ሀርድ የምታበዛ ሴት ስታጋጥመኝ በግድዋ ስለማወጣት ነው፡፡ ብቻ፣ሰው ማካበድ ስለሚወድ፣ የሆነ ስራ ስሰራ፣ የሆነ ስም ያወጣልኛል” የተጠርጣሪው መዝናናት መርማሪውን አስገርሞታል፡፡

“እሺ ዋናው ስምህስ?”“ወርቁ በላቸው”“ያያት ስም?”“የእናቴን ነው የአባቴን?”“የአባትህ አባት..?”“ገመቹ”“እድሜ?”“እድሜዬ?”“አዎ እድሜህ ስንት ነው?”“ሀያ አምስት ቢሞላኝ ነው”“የትምህርት ደረጃህ?”“አንድ ጊዜ ካራቴ ተምሬያለሁ”“ማን ነው ያስተማረህ? የት ነው የተማርኸው?”“ያስተማረኝ ‹ዘንጥል› የሚባል ጉዋደኛዬ ነው።

ዋሺንግተን ዲሲ፣ ከዛ ሜሪላንድ ገባሁ፡፡ አትላንታም ውስጥ ለአራት ዓመት ተቀምጫለሁ፡፡ አትላንታ የመጣሁት የቤተክርስቲያን ሥዕሎችን ለመስራት ጨረታ አሸንፌ ነው፡፡ የሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ቤተክርስቲያንን ሥዕሎች ሠርቻለሁ፡፡ አትላንታን ሳየው ለሥዕል ጥሩ አገር መሆኑን ተገነዘብኩ፡፡ ፀጥ ያለ ነው፤ መኖሪያ ቤቶቹ ሰፋፊ ናቸው፤ ለስራ ይመቻሉ፡፡

እንዴት ወደዚህ ልትመጣ ቻልክ? ኒው ኦርሊንስ የሚኖር ሬስቶራንት ያለው

ጓደኛዬ ነው ከተማዋን እንዳይ የጋበዘኝ፡፡ ቤቱን ሲያሳድስ ሥዕሎች እንድስልለትም ፈልጐ ነበር፡፡ በኋላ ግን ልጁ ሃሳቡን ቀይሮ ወደ ኢትዮጵያ መጣ። አገሩን ሳይ በጣም ደነገጥኩ…ለሰው ለማስረዳት ያስቸግራል፤ ኑ እና እዩት ከማለት በስተቀር፡፡ የሰው ልጅ ነጻ የሆነበት ከተማ ነው፤ መጨናነቅ የሌለበት፡፡ ወዲያው ተመልሼ ሄድኩና እቃዬን ሸክፌ እየከነፍኩ ወደዚህች ስቴት መጣሁ፡፡

እንዲህ ስላስደነገጠችህ ከተማ እስቲ በደንብ ንገረኝ …

ሲጀመር ይህቺ ግዛት የፈረንሳዮች ነበረች። ፈረንሳይ ና አርት ያላቸውን ቁርኝት ማንም ያውቀዋል፡፡ አርት በደማቸው ውስጥ ነው፡፡ ኒው ኦርሊንስ ሰው ሲፈጥር፣ መፃሕፍት ሲያገላብጥ፣ አዳዲስ ሃሳቦች ሲያንሸራሽር የሚኖርባት ከተማ ናት። የማየው ነገር ሁሉ ሥዕል ነው፤ ዕድሜ ይስጠኝ እንጂ የኒው ኦርሊያንስን ከተማ ስዬ የምጨርሰውም አይመስለኝ፡፡ የአሜሪካ ከተሞች ለእኔ ሙያ እንዴት ናቸው እያልኩ አንዳንዴ እየተቀመጥኩ፣ አንዳንዴ እግረመንገዴን ሳልፍ …የማየት እድሉ ነበረኝ፡፡ ግን እንደዚህ ዓይነት ጥንታዊና ለአርቲስቶች የሚመች ከተማ አላየሁም፡፡ የቤቶቹ ዲዛይን የሚገርም ነው። የምታያቸውን ቤቶች፣ አስፓልት፣ ድልድይ … ድንገት ብድግ ብለሽ ማደስ አትችይም፤ ክልክል ነው፡፡ ጥንታዊነታቸው ይፈለጋል፤ ይወደዳል፡፡ እዚህ አገር ሁሉም ቤት ዋይት ሃውስ ማለት ነው፡፡

የዛሬ ሁለት መቶ እና ሶስት መቶ ዓመት በልዩ ጥበብ የተሰሩ ናቸው፡፡ ቤቶቹን ብቻ በማየት የሚገኘውን ነገር…ሠዓሊዎች ይረዱታል፡፡ ስንማር እንደዚህ አይነት ቤቶችን ለማግኘት በጣም ከባድ ነበር፡፡ ጥንታዊ ቤቶችን እየፈለግን እንድንሰራ እንታዘዛለን፤ ዲኮራቲቭ ስለሆኑ፡፡ ዘይት ቀለም፣ ዋተር ከለሮች እዚህ እስከ ተፈጥሮዋቸው አሉ፡፡ በየመንገዱ ሙዚቃ ትሰሚያለሽ፡፡ ጃዝ አለ… ብቻ ምን ልበልሽ… በየመንገዱ በጊታር፣ በከበሮና በጃዝ አካባቢውን የሚያሳብዱት ተራ ሙዚቀኞች እንዳይመስሉሽ፡፡ በጣም ቶፕ (ታዋቂና ምርጥ) ሙዚቀኞች ናቸው፡፡ እዚህ ስቴት አንዴ ከታወቅሽ በቃ አገርሽ ይሆናል፡፡ ከ30-40 ሺህ የሚደርሱ ሠዓሊያን አሉ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሠዓሊዎች አንዱ ብሆን ምን ዋጋ አለው። ከ40ሺ ሠዓሊዎች ጋር እየሰሩ መፎካከር ግን ምን ያህል ፈታኝና አጓጊ እንደሚሆን አስቢው፡፡

አሜሪካ ከመጣህ በኋላ የሥዕል ትምህርት ቤት አልገባህም?

ቀሽሞች ናቸው፡፡ አትላንታ “ዲኬተር አርት ኢንስቲቲዩት” ለአንድ አመት ሄጄ እንዳየሁት፣ ጊዜ ከመፍጀት በቀር አንዳችም የሚጨምርልኝ ነገር አላገኘሁበትም፡፡ ለምን መሰለሽ? እኔ ዕውቀት ነው የምፈልገው፡፡ እነሱ ደግሞ “በትርፍ ጊዜህ ተማሪዎችን አስተምርልን”፣ “አንዳንድ ነገር አግዘን” አሉኝ፡፡ ሥዕል ለመስራት ጊዜ የሚሻማብኝ ስለሆነ አልፈለግሁም፡፡ ከአገር ቤት የተለየ የትምህርት አሰጣጥ አላየሁበትም፡፡ እንደውም የወረደ ነው። የሁለተኛ ዓመት ተማሪዎች የተባሉትን ሳያቸው በጣም ነው ያፈርኩት፡፡ ከቀን ተማሪዎች ይልቅ የማታ የሚማሩት ይሻላሉ፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ በሥዕል ሙያ ብቻ መተዳደር ከባድ ነው ይባላል፡፡ እዚህስ?

አየሽ..ይሄ አገር ያደገ ነወ፡፡ ኒው ኦርሊያንስ ሥዕል የሚከበርበትና የሚደነቅበት የጥበብ ከተማ ነው፡፡ እዚህ ሥዕል ሲገዙ በክሬዲት ካርድ ነው፡፡ ኦንላይን ነው አልኩሽ የምቸበችበው፡፡ በነገራችን ላይ

ይሄ ሁሉ የምታይው ሠዓሊ ሥዕል የሚስለው ፈቃድ አውጥቶ ነው፡፡ የሙያ ፈቃዳችንን ከጀርባ ሸጉጠን ነው የምንስለው፡፡ ተቆጣጣሪዎች እየዞሩ ፈቃድ ይጠይቃሉ፡፡ ከአሁን በኋላ ግን ፈቃድ አንሰጥም፤ ሞልቷል ብለዋል፡፡ አንድ አርቲስት ኒው ኦሪሊያንስን አንድ ጊዜ ካየ፣ ሌላ የትም ቦታ ንቅንቅ አይልም፡፡ ለሠዓሊ የሚመች ከተማ ነው፡፡

ወደ ኒው ኦርሊንስ ስመጣ ያረፍኩበት ሰውዬ ባለ ሶስት ፎቅ ቤት ነበረው፡፡ ሁለቱን ፎቅ ለሶስት ወር ዘግቼ ሥዕል እንድሰራበት ሰጠኝ፡፡ ሰባ ሥዕል ነው ጨርሴ የወጣሁት፡፡ ኤግዚቢሽን እንዳሳይም አመቻቸልኝ፤ ከዛ በኋላ ጋለሪዎች፣ የሥዕል መደብሮች ሊያስቀምጡኝ ነው፡፡ ብዙ ስቴቶች ኤግዚቢሽን እንዳሳይ ጠይቀውኛል፡፡ ባለፈው ወር ዲሲና ኒውዮርክ አሳይቼ ነው የመጣሁት፡፡

ስራዎችህ ምን ዓይነት ጭብጦች ላይ ያተኩራሉ?በአብዛኛው …ሰሚ አብስትራክ ናቸው፡፡ ኒው

ኦርሊያንስ ከመጣሁ በኋላ ግን…እንደ ማዴግራ፣ ጃዝ፣ ዞዳ ዳንስ የመሳሰሉትን የዚህ አገር ሰው የለመዳቸውና የሚያውቃቸውን ታሪካዊና ባህላዊ የሆኑ ነገሮች አካትቼ ነው የምሰራው፡፡ እዛው ተስሎ እዛው ነው የሚሸጠው፡፡ በጃክሰን ስኩዌር ስንስል ያየሽን “ፓይረትስ” እንባላለን፡፡ እንደተመለከትሽን በአራት መዓዘን ዙሪያውን ከበን ነው የምንሰራው። በእኔ መስመር ያሉት ወደ አስራ ሁለት ይጠጋሉ። ከሩሲያ፣ ከጀርመን፣ ከኒው ኦርሊንስና ከተለያዩ ስቴቶች የመጡ ናቸው፡፡ ቦታው ላይ ፕሪንት አይሸጥም፤ እዛው ተስሎ እዛው ነው የሚሸጠው። ይሄንን የሚቆጣጠሩ አሉ፡፡ ይገርምሻል ስዬ የማልጨርሰው ሁለት ሳጥን ስኬች ነው ያለኝ፡፡

“ወዲያው ተስሎ ወዲያው” ስትል በትዕዛዝ ማለትህ ነው?

አዎ አንዳንዱ መጥቶ ያዝሻል…ላንድ ስኬፕ ስራልኝ፣ ፎቶ ስራልኝ ይላሉ፤ ቁጭ ብሎ ሳለኝ የሚልም አለ፡፡ ቤት ውስጥ የሰራኋቸውን ኦሪጂናል ሥዕሎች መግዛት የሚፈልጉ ስላሉ ይዣቸው

እሄዳለሁ፡፡ ከዓለም ዙሪያ የሚመጡ ቱሪስቶች ስለሚበዙ ሥዕሎቹን ሲያይዋቸው ያውቋቸዋል። ከሥዕሎቹ ጋር በመንፈስ (spiritually) ነው የሚግባቡት፡፡

ሥዕሎችህ ኢትዮጵያዊ ባህል ወይም ታሪክ የሚያንፀባርቅ ነገር አላቸው?

ኢትዮጵያ እያለሁና ፒትስበርግ፣ ሲሊቫኒያ ከመጣሁ በኋላ የሰራኋቸው በከፊል የኢትዮጵያን ነገር ያንፀባርቃሉ፡፡ እዚህም ሆነ በየስቴቱ ፈረሶች የተለመዱ ናቸው፡፡ ስለዚህ ሥዕሎቼ ላይ ፈረሶች ይበዛሉ፡፡ አገር ቤትም እያለሁ ፈረሶች በብዛት እሰራ ነበር፡፡ ማንኛውም ሰው ይገዛቸዋል፡፡ አንዳንዱ ደግሞ የአድዋን ታሪክ ጠይቆ የሚገዛ አለ፡፡

ሰዎች ስለ ሥዕል ስራዎችህ ምን ዓይነት አስተያየት ይሰጡሃል?

በነገርሽ ላይ የአዲስ አበባ ስነጥበብ ትምህርት ቤት በአፍሪካ የመጀመሪያው የሥዕል ትምህርት ቤት ነበር፡፡ ሥዕሎቼን በተመለከተ ብዙዎች በጣም ነው የሚደነቁት፡፡ “ኢትዮጵያዊ ሆነህ እንዴት እንደዚህ መስራት ቻልክ?” እያሉ በመገረም ይጠይቁኛል። ይሄን ለማስረዳት ይከብዳል፡፡ ግን የሚያሳፍረኝ ሳይሆን የምደሰትበት ነው፡፡ የትም ቦት ሄጄ ሰዎች በሥዕሎቼ ሲደነግጡ አስተውላለሁ፡፡

በቅርቡ ልትሰራ ያሰብካቸው ነገሮች አሉ?ወደ ኒው ኦርሊንስ ከመጣሁ አምስት ወሬ ነው።

ለፈረንጆች አዲስ ዓመት (በጃንዋሪ) ኤግዚቢሽን ላሳይ እየተዘጋጀሁ ነው፡፡ ስቶሮች (የሥዕል መሸጫ መደብሮች) ሥዕሎቼን በብዛት እንዳቀርብላቸው ይጠይቁኛል፡፡

በከተማዋ ውስጥ ባሉ መጠጥ ቤቶች (ባርስ) ብዙ ሥዕሎቼ ተሰቅለው ታገኛለሽ። ስሜና አድራሻዬ ተጽፎባቸዋል፡፡ ይሄንንም አይተው ነው “ፎክስ ቻናሎች” ደውለው ቃለ መጠይቅ ያደረጉልኝ። ኤግዚቢሽን ሳደርግ ሮጠው ነው የሚመጡት። በአለም አቀፍ መድረክ አገሬን ለማስጠራት ጥሩ አጋጣሚ እየሆነልኝ ነው፡፡

የተማርሁት እንጦጦ ጫካ ውስጥ” የመርማሪው ጆሮዎች ይበልጥ ተቀሰሩ፡፡

“ዘንጥል ማነው? አሁንስ የት ነው ያለው?”“ትላንት ደየመ፡፡ እንዴት ያለ ጎበዝ ልጅ ነበር

መሰለህ!”“በምን ምክንያት ሞተ?” መርማሪው እንደ ዋዘ

ጠየቀው፡፡“አንድ ከእሱ የባሰ ጉልቤ በስኪኒ ወጋና ገደለው።

እኔ እንኩዋ ከእሱ ጋር መሳፈጥህን ተው ብየው ነበር”“እሺ ስራ?”“ምን አይነት ስራ?”“ስራህ ምንድነው? ነው የምልህ!” መርማሪው

በተሰላቸ አንደበት ጠየቀው፡፡“የተገኘውን ነው የምሰራ”“ለምሳሌ?”“በቃ፣ ቋጠሮም ተገኘ ሌላ የጉልበት ስራ

እሰራለሁ”“የጉልበት ስራ ስትል?”“ያው እ…ሞባይል፣ቦርሳ፣እ..አንዳንዴ ሀንግ…”

አንገቱን በግዴለሽነት ሰበቀ፡፡“ሞባይል፣ቦርሳ ትነጥቃለህ፡፡ ‹ሀንግ አረጋለሁ›

ስትል ምን ማለትህ ነው?”“ይህ ጠፍቶህ ነው? ያው ፍሉስ አለው ብዬ

የገመትሁትን ሰው አፍኜ እዳብሰዋለሁ”“እዳብሰዋለሁ?” መርማሪው ትኩር ብዬ እያየ

ጠየቀው፡፡“አዎ፣ ኪሱን እፈትሻለሁ”“አልሰጥም ብሎ ቢታገልህስ?”“ዋጋውን ያገኛላ”“ማለት?”“ኪል አረገዋለሁዋ”“ጥሩ፣የቅድሙን ሰውዬ ታውቀዋለህ?”

“የቱን?”“ሀዳስ ቤት ወድቆ የተገኘውን”ከዛሬ በፊት አላውቀውም”“ታዲያ ለምን መታኸው?”“ሲመታት እያየሁ ዝም ልበል?”“እንዴት?”“እንዴትማ..ሲቅለበለብ መጥቶ፣ለሾርት አምስት

ብር ከፈላት”“እሺ..?” ፖሊስ እያንዳንድዋን ቃል በጥንቃቄ

መመዝገብ ጀመረ፡፡“ከዚያ፣ አልጋ ላይ ወጣና ቢለው፣ ቢለው

አልቆምለት አለ፡፡ በዚህ የተነሳ፣ ብሬን መልሽልኝ አልመልስም፣ ከሀዳስ ጋር ጭቅጭቅ ጀመረና እንደማትመልስለት ሲያውቅ ይደበድባት ጀመር፡፡ በዚህ የተነሳ ያው…በቃ በቦክስ ስሰጠው ሳጥኑ ላይ ወደቀ”

“ሲመታት እንዴት አየህ?”“እዚያው ነበርሁዋ”“የት?”“ከምስጢር ክፍልዋ”“ከማን?”“ከሀዳስ ነዋ”“ምን ልትሰራ?”“ቢዝነስ ነዋ”“ምን አይነት ቢዝነስ?”“ያው እሱ ችክ አገኘሁ ብሎ ሲያፎደፍድ፣እኔ

ኪሱን እፈትሻለሁ”“ብዙ ጊዜ እንዲህ ታረጋለህ?”“አዎ በቸሰትሁ ጊዜ ሁሉ እሰራለሁ”“ለመሆኑ ሀዳስ ምንህ ናት?”“ሚስቴ”“ሚስቴ?” መርማሪ ፖሊስ ተገረመ፡፡

“አዎ ሚስቴ፡፡ ምነው?”“አንተ አልጋ ላይ ፣ሚስትህ ከሌላ ወንድ ጋር

ስትተኛ ትንሽ አትናደድም?” “ምን ሀርድ አለው? ነካው እንጂ፣እንዳለ ይዞብኝ

አይሄድ፡፡ ወዲያውስ፣ቢዝነስ እኮ ነው”“ቢዝነስ?”“አዎና ቢዝነስ”“እንዲህ የምታደርጉት ተስማምታችሁ ነው?

ወይስ እያስገደድሀት?”“ለምን አስገድዳታለሁ? ለቢዝነስ አይደል እንዴ

ካገርዋ የመጣችው?”“የፈፀምኩት ድርጊት ትክክል ነው ብለህ

ታስባለህ?”“ቢዝነስ ስትሰራ’ኮ፣ ያው መሳሳትህ አይቀርም”“እና? ተሳስቻለሁ ነው?”“ባልሳሳትም ያው መትቸዋለሁ፡፡ ፊልም

አታይም እንዴ? ለቢዝነስ ሲባል ስንት ወንጀል ነው የሚሰራ?”

“እና ፊልም ላይ ያየኸውን ለመድገም ስትል፣ የምስጢር ቦታ አዘጋጅተህ ሚስትህን ከሌላ ወንድ ጋር እንድትማግጥ ታረጋለህ፡፡ በአጋጣሚውም ዘረፋ ታካሂዳለህ?”

“ዘረፋ አይደለም፤ ቢዝነስ ነው፡፡ ቆይ እስኪ? አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ፤ ሚስት አለህ የለህም?”

“አለችኝ”“ጥሩ፣ ስራስ አላት?”“የላትም” ፖሊሱ መጨረሻውን ለመስማት ጓጓ።“በጣም ጥሩ፣ ስራ ከሌላት መቼም ዝም ብለህ

ስትቀልባት አትኖርም፡፡ ቀን ቀን ቢዝነስ ስትሰራ ብትውልኮ ማታ የአንተው ናት፡፡ እ….”

“በቃ…!”መርማሪው ድንገት አንባረቀበትና ወደ ማረሚያ ቤት ላከው፡፡

Page 24: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 24

መፅሐፍ ከገፅ 17 የዞረምርመራ ከገፅ 5 የዞረ

የወጣት በረከት ክንፈ ገ/እግዚአብሔር የ80 ቀን መታሰቢያ ጥቅምት 10/2006 ዓ.ም በቦሌ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን በፀሎተ ፍታትና ነደያንን በመዘከር ታስቦ ይውላል፡፡

በደረሰብን መሪር ሀዘን ምክንያት ከጎናችን በመሆን ከሃገር ውስጥና ከሀገር ውጪ በስልክ፣ በደብዳቤ እንዲሁም ቤት ድረስ በአካል በመምጣትና በመመላለስ ላጽናናችሁን ሁሉ በልዑል እግዚአብሔር ስም ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

የወጣት በረከት ክንፈየ80 ቀን መታሰቢያ

“የጌታ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን” ሐዋ 21፣14

ሰኔ 27/1977- ሐምሌ 28/2005 ዓ.ም

የወንድማችንን ነፍስ ከሚወዱት ቤተሰቦቹ አጠገብ ልዑል እግዚአብሔር በገነት ያስቀምጥልን፡፡ ቤተሰቦቹ

መልስ1. ሃላፊ ደስታ2. ማንኛውም ነገር የማይቃናለት3. ፅድቅ4. ልጃገረድ አጨ5. ብቻውን አይበላም6. ኮከባቸው የሚገጥም7. የአንገት እስክስታ8. ጨርሽው (ለአዲስ ልብስ)9. እብድ10. ተበተ

አስቀድሞ ለጉብኝት ካናዳ ሄዶ በነበረበት ጊዜ፣ ከአንድ ጌጣጌጥ መደብር ለመገብየት ገብቶ ሳለ፣ ሻጭቱ “ለአንተ የሚሆን ልዩ ዕቃ ና ላሳይህ” ብላ ወደ ሌላ ክፍል ወስዳው ከብር የተሰራ የእሥራኤላውያን ቀንደ መለከት ሥል የተንጠለጠለበት ጌጥ፣ ከታቦቱ ጋር የማይጠፋ እንደነበር ገልጻለት፣ እንዲገዛ አድርጋው ነበር፡፡

ጂም ራንኪን በዚህ የጌጣጌጥ መደብር ውስጥ ይህን ከገዛበት ዕለት በፊት በነበረው ሌሊት ነው በእንቅልፉ ውስጥ ሳለ፣ የቃልኪዳኑን ታቦት ለምን እንደማይፈልገው የተጠየቀው፤ እሱ እንደተረከው። ደንግጦ ባነነ፣ ያ ጥያቄ ሲያስጨንቀው ቆየ፡፡ ጧት ተነሳ፣ ከውሎው ተመልሶ ጌጣጌጥ ሊገበይ በገባበት ነበር፣ ያ የቀንደ መለከቱን የብር ጌጥ የገዛው፡፡ በጣና ቂርቆስ ገዳም ከነዚያ ንዋያት በተጨማሪ ኢየሱስ ከእናቱ ጋር እዚያ እንደተቀመጠ የሚተርከውን መጽሐፍም አሳዩአቸው፡፡ ራንኪን ጥቂት ገጾችን ፎቶ አነሳ፡፡

በዚሁ የኢትዮጵያ ቆይታቸው አብቅቶ አሜሪካ ሲገቡ፣ ያን በፎቶ የያዙትን የግእዝ ቃል ተርጓሚ ፈለጉ፡፡ ያገኟቸው ኢትዮጵያዊ ቄስ አስቀድሞ እንደተገለፀው ያንኑ ታሪክ የሚናገር መሆኑን ገለፁለት፡፡

አበቃ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በኢትዮጵያ የቱ ጋ ነው ያለው?

ይሄን ሾላ በድፍን የተወበትን መጽሐፍ ነው “ኢየሱስ ክርስቶስ በኢትዮጵያ” ሲል የሰየመው። መጽሐፉ ከዚህ ይልቅ ሌሎች ዓላማዎች የያዘ ይመስላል፡፡ በአክሱምና በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ወንጌልን የመስበክ ፕሮጀክት አብረው ከተጓዙት ጋር ሲነድፉ ይገኛሉ፡፡ ከሁሉ ሁሉ የሚያስገርመው ግን ኢትዮጵያውያንን ለመስደብ እና ለመንቀፍ የመቸኮሉ ነገር ነው፡፡ በስንቱ መጽሐፍ ተጽፎ፣ በየጊዜው እየተገለፀ የሚገኘውን ይህን ጉዳይ፣ “ለምንድነው የሚደብቁት” እያለ በተደጋጋሚ ይቆጣል፡፡

ይሄም ሳያንሰው እግዚአብሔር እንዴት “በዚች ውኃዎቿ ሁሉ በበሽታ የተበከለ…” አገር የቃል ኪዳን ታቦቱን የመሰለውን ሊደብቅባት ቻለ? በማለት ሕዝቡንና ሀገሪቱን ይሰድባል፡፡

ምናልባት የዚህ መጽሐፍ አንድ ጥቅም ተደርጐ ሊወሰድ የሚችለው፣ ፀሐፊው በደርዘን ፓንቶችና ካልሲዎች ሳይቀር ወሻሽቆ በሻንጣው ደብቆ ያወጣቸውን ዓይነቶች የቅርሶች ዝርፊያ እንደሚፈፀም እና ጥበቃው ምን ያህል ልል እንደሆነ ማሳየቱ ብቻ ይመስለኛል፡፡

ሌሎች መፅሃፉን ያነበቡ ሰዎች ግን “ቢያንስ ኢየሱስ ክርስቶስ በኢትዮጵያ” እንደነበረ መገለጹን እንደ አንድ ጥቅም ቆጥረውታል፡፡

ግና የታለና እሱ?

፡ ፖሊስ አስከሬኑን አምጥቶ አስመረመረ። ወጣቱ በመኪና አደጋ ሳይሆን በሳንባ ምች እንደሞተ በአስክሬን ምርመራ ስለተረጋገጠ፣ የተሳሳተ ጥርጣሬና ውንጀላን ለማስወገድ ተችሏል።

በሌላ በኩል ደግሞ ወንጀለኞች ማምለጫ እንዳያገኙ ለመከላከል የአስከሬን ምርመራ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው፡፡ እራሱን አጥፍቷል የተባለ ሰው፣ አስከሬኑ ሲመረመር በሌላ ሰው እጅ እንደሞተ የሚረጋገጥበት አጋጣሚ አለ፡፡ ያኔ ፖሊስ ወንጀለኛውን አድኖ ይይዘዋል፡፡

የአስከሬን ምርመራ በአንድ ሆስፒታል ውስጥ ብቻ መሰጠቱ ችግሮችን ይፈጥራል ያሉት አቶ ሞገስ፤ ተገልጋዮችንም የሚያጉላላ እክል በየጊዜው ሊፈጠር ይችላል ይላሉ፡፡ በአንድ ወይም በሁለት ባለሙያዎች ብቻ የሚካሄድ የአስከሬን ምርመራ፣ ባለሙያዎቹ የግል ችግር ሲገጥማቸው ስለሚስተጓጎል ተገልጋይ ይጉላላል። በተለይ አስክሬን ለመውሰድ መኪና ተከራይተው ከክልሎች የሚመጡ ቤተሰቦች ከፍተኛ የገንዘብና የህሊና ጉዳት ይደርስባቸዋል፡፡

የአስክሬን ምርመራ ባለሙያዎች በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አማካኝነት ከኩባ ብቻ የሚመጡት በክፍያቸውም ተመጣጣኝነት ሊሆን ይችላል የሚሉት አቶ ሞገስ፤ በባለሙያዎች እጥረት አገልግሎት የተስተጓጎለው ለሁለት ቀናት ብቻ ነው ብለዋል፡፡ የአገልግሎቱ መስተጓጎል ተጋኖ የወጣው ህብረተሰቡ የጉዳዩን አሳሳቢነት ስለተገነዘበ ይመስለኛል ሲሉም አቶ ሞገስ ተናግረዋል፡፡

መንግስት ከገፅ 10 የዞረማራመድን ያስቀድማሉ ይለናል። ስለዚህም ይላል፤ ለማህበረሰቡ ሲሞግት መንግስታት ለማይገረሰሰው የህዝብ ዳኝነት በአያሌው/ፍጹም ረዳቶች መሆን ይገባቸዋል፤ ስለሆነም የመንግስታት ቅርጽ እንደየ ማህበረሰቡ ስሪት ተስማሚ መዋቅር ሊኖራቸው ይገባል። ይህም ማለት የኛ ዘመናዊ/መደበኛ መንግስታችን የማህበረሰቡን ጥቅም ያስከብር ዘንድ የማህበረሰቡን እሴቶች የሚመስሉ መዋቅሮች ሊኖሩት ይገባል ማለት ነው። ይህንን ለማድረግ

ቱሪስት ከገፅ 9 የዞረለማስትሬት ዲግሪ ማሟያቸው እ.ኤ.አ በ2013 “Tourist Destination competitiveness of Ethiopia; The Tour operators perspective” በሚል ርእስ ባቀረቡት ጥናት ማጠቃለያ ላይ፤ “ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ዐውደርእይ ላይ ስትሳተፍ ከፖለቲከኞች ይልቅ ገበያ ሊያመጡ በሚችሉ የዘርፉ ባለሙያዎች ብትወክል ይበጃታል” ብለዋል፡፡ መካከለኛው ምስራቅ በተለይም የዓረቡ ዓለም የተዘነጋ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ገበያ ክልል እንደሆነም በጥናታቸው ጠቁመዋል፡፡ ሚኒስቴሩ አምና ባሳተመው መጽሔት ላይ ኢትዮጵያን ከሚጐበኙ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶች ውስጥ 51.2 በመቶ የሚሆኑት የአሜሪካ፣ ቻይና፣ እንግሊዝ፣ ጀርመን፣ ኬንያ፣ ጣሊያን፣ ሳኡዲ አረቢያ፣ ሕንድና ፊንላንድ ዜጐች መሆናቸውን ያመለክታል፡፡

ችግሩ ግን እነዚህ ቱሪስቶች በሚጎበኟቸው ስፍራዎች አብዛኛውን ጊዜ የሚቀበሏቸው አስጐብኝዎች በቂ እውቀትና ልምድ የሌላቸው ከማስጎብኘት ይልቅ ከማገት የሚስተካከል ሚና የሚጫወቱ ወጣቶች እንደሆኑ ጥናቶች ያሳያሉ። በዚህም የተነሳ በዓመት ግማሽ ሚሊዮን እንኳን ያልደረሱት የኢትዮጵያ ጎብኚዎች በአገሪቱ ውስጥ ያላቸው ቆይታ በጣም ውሱን ነው፡፡ እስራኤል በቱሪስት ብዛት ቀዳሚ ከሆኑትን ፈረንሳይ እና አሜሪካ ጋር ልትወዳደር አትችልም፡፡ ነገር ግን የቆይታ ጊዜአቸውን በማራዘም ከቱሪዝም ዳጎስ ያለ ገቢ እንደምታገኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ። አንዲት ትንሽዬ የእስራኤል ከተማን በቅጡ

ጐብኝቶ ለመጨረስ ቀናት እንደሚፈጅ ይነገራል። ኢትዮጵያም የእስራኤልን ፈለግ የመከተል ብርቱ ጥረት ልታደርግ ይገባል፡፡ ለዚህ ደግሞ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና መንገዶችን በስፋት በመገንባት የጉብኝት ስፍራዎችን ለማብዛት መትጋትን ይጠይቃል፡፡

ከዚሁ ጐን ለጐን የኢንተርኔት አገልግሎቶችን በተለይ የቱሪዝም መስህብ በሆኑ ስፍራዎች ማስፋፋት ብቻ ሳይሆን ፈጣንና ቀልጣፋ ማድረግም የግድ ነው፡፡ ባለፈው ሰኔ ወር መጨረሻ፣ የኮንሶ አካባቢ ዓለም አቀፍ መካነ ቅርስ የሆነበት አንደኛ ዓመት ሲከበር፣ በርካታ የውጭ ሀገር ጎብኚዎች የኢንተርኔት አገልግሎት ለማግኘት አርባምንጭ ድረስ ለመጓዝ መገደዳቸውን ታዝቤአለሁ፡፡

በቂ የቱሪዝም እውቀትና ልምድ የሌላቸው አስጐብኝዎች፣ መስተንግዶአቸው እንደነገሩ የሆኑ ሆቴሎች፣ ደካማና ፈዛዛ እንቅስቃሴ ይዘን ከአፍሪካ ምርጥ አምስት የቱሪዝም መዳረሻ አገራት አንዱ ለመሆን ማሰብ ከህልምነት አያልፍም፡፡

የቱሪዝም ኢንዱስትሪው በአንድ ወገን ጥረትና ትጋት የታሰበበት ደረጃ ላይ ሊደርስ አይችልም። ከግሉም ሆነ ከመንግሥት ዘርፍ የለያዩ ወገኖች ተዋናይ የሆኑበት ሰፊ ክፍለ ኢኮኖሚ በመሆኑ የተቀናጀ የጋራ ስራን ይፈልጋል፡፡ ከልብ መትጋትን ይጠይቃል፡፡ ያኔ የታቀደውም ሆነ የታለመው ሊሳካ ይችላል፡፡ በተለይ ደግሞ ራሳችንን በማስተዋወቁና በመሸጡ በኩል እጅግ ብዙ የቤት ሥራ እንዳለብን ማወቁ ተገቢ ነው፡፡

ግን የታደልን ማህበረሰብ ነን ብዬ አላምንም። ከማህበረሰባችን እሴቶች ጋር የሚጋጩ ሁልቆ መሳፍርት ችግሮችን እያስተዋልን ነው።

መቼ ተንሻትተን ነው ግን እዚህ ደረጃ የደረስነው? ከመቼው የሃያ ሺህ ብር ሎተሪ የመጀመሪያ እድል ከሚደረግባት ሃገር ወደ አራት መቶ ሺህ ብር ወርሃዊ የቤት ኪራይ የሚከፈልባት ሃገር ደረስን። በአስር ሺዎች ከሚቆጠር የጎዳና ተዳዳሪዎች ወደ መቶ ሺዎች አድገናል እኮ። ኢትዮጵያዊነት/ፍቅር ወዴት ዘመም ዘመም ነው ያለች አዝማሪ? ያንጀትን እንዴት ቢናገሩት እንግባባ ይሆን። እንዲህም ይለናል ሩሶ፤ ገዥዎች ስልጣናቸውን የበለጠ ለማጠናከር ማህበረሰባችን ሰላማዊና የተረጋጋ መሆን አለበት፤ ይህንንም ለማሳካት ደግሞ መንግስት፣ህግ እና ቅጣትም ያስፈልገናል። ገዥዎች ይህንን የሚያደርጉት ግን መብትና ፍትህ ለማስከበር ሳይሆን ያልተገባ ጥቅም የሚያገኙበትን መንገድ ለማስጠበቅና ደካማውን የበለጠ ለመጨቆን ነው ይለናል። አንድ የድሃ እንጉርጉሮ ትዝ አለኝ፤ ልማታዊ መንግስታችን የዘነጋንን እኛን ድሆቹን ይወክላል ይመስለኛል።

ያለው ስጋ ይብላ፤ እየዘለዘለ በስለታም ቢላየሌለው ባቄላ፤ ሲሻው እያሾቀ ሲሻው እየቆላ

ይህ ነው የድሃ እንጉርጉሮ። ዛሬ ዛሬ ግን ባቄላውንም የምናገኘው አንመስልም፤ በዚህ አካሄዳችን። ባቄላውን የሚያስከብርልን መዋቅር ያስፈልገናል ለዚህ ደግሞ ፈሪሃ ፈጣሪ ካላቸው ከትንሹ መንግስት/የየአካባቢው ሽማግሌዎች ውክልና ውጭ የሚበጀን አናገኝም።የፌደሬሽን ምክር ቤት ሳይሆን የሽማግሌዎች ምክር ቤት ያስፈልገናል። ርዕሰ ብሔሩም መመረጥ የሚገባው ከሃገር ሽማግሌዎች ምክር ቤት መሆን አለበት። አማርኛው እያጠረኝ ነው መሰለኝ እና በሚከተለው የሩሶ እንግሊዝኛ ሃሳቤን ላጠቃልል።

To renounce liberty is to renounce being a man, to surrender the rights of humanity and even its duties. For him who renounces everything no indentify is possible. Such a renunciation is incompatible with man’s nature; to remove all liberty from his will is to remove all morality from his acts. Finally, it is an empty and contradictory convention that sets up, on the one side, absolute authority, and, on the other, unlimited obedience.

የወ/ሮ ወርቅሸት ከበደ የ40 ቀን መታሰቢያ እና ሐውልት

ምርቃት ጥቅምት 10 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡

00 ሰዓት በቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ

ቤ/ክርስቲያን በፀሎትና በፍትሐት ታስቦ ይውላል፡፡

ከቤተሰቦቿ

የወ/ሮ ወርቅሸት ከበደ የ40 ቀን መታሰቢያ

“በሞት ጥላ መካከል እንኳን ብሄድ አንተ ከኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም” መዝ 22፡23-4

Page 25: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 25 ህይወት ከገፅ 14 የዞረሲስተሞች በጭራሽ አይገናኙም፡፡ ስለዚህ፣ እናቲቱ

የምታስበው ወይም የምታየው ነገር ሽሉን በፍፁም አያውከውም፡፡ ስለዚህ፣ ሰው አካል ላይ ጠቆር ወይም ነጣ ያለ ነገር ሲኖር፣ “እናቱ እሷን ወይም እሱን እርጉዝ ሆና የሆነ ነገር ሲያምራት የዳበሰችው ወይም የነካችው ቦታ “ሽታ” ነው” የሚለው ብዙ ዘመናት ያስቆጠረው አፈ-ታሪክ ውሸት ነው ማለት ነው። የሽሉ የነርቭ ሲስተም፣ በእናትየው ጋር በፍፁም እንደማይገናኘው ሁሉ፣ የደም ዝውውር ሲስተሙም ከእናቱ ጋር ፈፅሞ የተለያየ ነው። ሽሉ፣ ከእናቱ ጋር በጭራሽ የማይገናኝና የራሱ የሆነ ደም ነው የሚያመርተው፡፡ ሁለቱ የደም ዝውውሮች (እናትና ሽሉ) ኦክስጅንም ሆነ ምግብ የሚለዋወጡት፣ በእርግዝና ወቅት በማኅፀን ውስጥ በሚፈጠርና እንደተወለደ በሚበጠሰው እትብት ነው፡፡ በሽሉ እንብርት ላይ ተጣብቆ የሚገኘው እትብት ከ12 እስከ 15 ሳ.ሜ ርዝመት ሲኖረው፣ ቪሊ በተባሉ ጥቃቅን የደም ስሮች የተሠራ ነው፡፡ የሽሉ መተንፈሻና ምግብ መፍጫ ሲስተሞች ዕድገት ዘገምተኛ ነው፡፡ ስለዚህ፣ ወደፊት የሚወለደውን ልጅ ወክሎ የሚተነፍሰውና ምግብ የሚፈጨው እትብት ስለሆነ ለ ሽሉ የሚሰጠው ጥቅም እጅግ ከፍተኛና በዋጋ ሊተመን የማይችል ነው፡፡

እናቲቱ የሽሉ እንቅስቅሴ የሚሰማት በአራተኛው ወር መጨረሻ ገደማ ነው፡፡ መጀመሪያ አካባቢ እንቅስቅሴው በጣም ደካማ በመሆኑ የሽሉ እጅና እግር እንቅስቃሴ ጠንከር ለማለት ሳምንታት ሊወስድ ይችላል፡፡ አሁን በእርግዝናው አጋማሽ ነን እንበል፡፡ በዚህ ጊዜ ሽሉ 15 ሳ.ሜ ርዝመትና 170 ግራም ክብደት ይኖረዋል፡፡ ቅንድብና ሽፋሽፍቱ መታየት ይጀምራሉ፡፡ የልብ ምቱ ጠንከር በማለቱ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በልብ ምት ማዳመጫ (ስቴትስኮፕ) ሊሰማ ይችላል፡፡ ልቡ በአንድ ደቂቃ 136 ጊዜ ይመታል፡፡ ይህም የእናቱን ልብ ምት እጥፍ ያህል ማለት ነው፡፡

ሽሉ ፣ በ6ኛው ወር መጨረሻ አንድ ማስመርያ ያህል ርዝመትና ግማሽ ኪ.ግ ያህል ክብደት ይኖረዋል፡፡ በዚህ ጊዜ፣ ሲታፈን ድምፅ ማሰማት፣ የፊት ጡንቻዎቹን ማንቀሳቀስና ማስነጠስ ይችላል። ዓይኖቹ የተሟላ ዕድገት ላይ ቢደርሱም፣ ብርሃን ብቻ ነው የሚለዩት፡፡ አሁን ሽሉ በሚያስደንቅ

ሁኔታ ጥንካሬ በማምጣት፣ አካሉን መዘረጋጋትና እራሱን ማገላበጥ ይችላል፡፡ የደረት ጡንቻዎቹ በየዕለቱ ለመተንፈስ በሚያደርጉት ዝግጅት ይበልጥ እየጠነከሩ ነው፡፡ ኩላሊቶቹ ለማጣራት፣ አንጀቱ ምግብ ለመፍጨት ዝግጁ ቢሆኑም፣ ቆሻሻ ማስወገጃ ስለሌለ መደበኛ ሥራቸውን የሚጀምሩት

ልጁ ሲወለድ ነው፡፡ ሽሉ ከተወለደ በኋላ የተፈጥሮ ግዴታ የሆነውን አበላል ለመለማመድ (ያለ ማቋረጥ ማለት ይቻላል) የመጥባት እንቅስቅሴ ያደርጋል፡፡ አንዳንድ ልጆች ከመወለዳቸው በፊት እንደሚያደርጉት አውራ ጣቱን ሊጠባ ይችላል፡፡

በዘጠነኛው ወር መጨረሻ አካባቢ ወይም በ252ኛው ቀን ገደማ ሽሉ የሆድ ውስጥ ዕድገቱን ጨርሶ ለመወለድ ዝግጁ ይሆናል፡፡ ፅንስ ተፈጥሮ ለመወለድ 267 ቀናት ይፈጃል የሚባለው አማካይ ስሌት ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ልጁ “ይወለዳል” ተብሎ ከሚጠበቅበት ቀን፣ 15 ቀናት ቀድሞ ወይም ዘግይቶ ሊወለድ ይችላል፡፡

ሊወለድ የደረሰ ሽሉ ብዙውን ጊዜ ከ2 ተኩል እስከ 3 ኪ.ግ ሲመዝን፣ 48 ሳ.ሜ ወይም አንድ ማስመሪያ ያህል ቁመት ይኖረዋል፡፡ በማኅፀን ውስጥ ያለው ቦታ እንዲበቃው፣ የእጁን ክንዶች ደረቱ ላይ አጥፎ ሲያስቀምጥ፣ ጭኖቹን ደግሞ ኩርምት ብሎ ሆዱ ላይ ያኖራል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ እንቅልፍ ላይ የሆነ ይመስል ፀጥተኛ ነው፡፡ ነገር ግን አሁን፣ እጅና እግሮቹን ሲያንቀሳቅስ እናቲቱ የሚሰማት ግፊት ኃይለኛ ነው፡፡ እርግዝናውን የሚከታተለው ሐኪም ሽሉ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ ለማወቅ፣ የእጁን መዳፍ እናቲቱ ማህፀን ላይ ቢያሳርፍ ሽሉ ዝም የሚል እንዳይመስላችሁ፤ እጁን በማወራጨት የቦክስ ምላሽ በመስጠት ተቃውሞውን ይገልፃል፡፡

በዚህ ጊዜ ሽሉ ትንሽ፣ ነገር ግን የተሟላ የሰው ልጅ ፍጡር ነው፡፡ አሁን፣ በማንኛውም ቀን ለመወለድ ወይም ወደዚች ዓለም ለመምጣት፣ ማንነቱን የሚፈታተን የመጀመሪያውን ፈታኝ ሁኔታ ይጋፈጣል፡፡ አሁን የሚጠበቀው የእሱ መምጣት ወይም መወለድ ነው፡፡ እናቱ ማኅፀን ውስጥ ሆኖ ያካበተውን የሚደንቁ ተግባራዊ ልምዶች ከተወለደም በኋላ ይቀጥላል፡፡ በአጭሩ፣ የማንኛውም ሰው ሕይወት፣ ከመወለዱ በፊት ይህን ነው የሚመስለው፡፡

በላይአብ ከገፅ 16 የዞረቴስት) ይገባል፡፡ መስተዋቶች፣ በሮች፣ … በትክክል ካልተገጠሙ፣ ውሃና አቧራ ሊያስገቡ ይችላሉ። ስለዚህ፣ መኪናው ከስርም ሆነ ከላይ ኃይለኛ ግፊት ባለው ውሃ ውስጥ ይገባል፡፡ በዚህም ጊዜ ስህተት ከተገኘ እንደገና ወደ ኋላ ተመልሶ ስህተቱ ይታረማል። የመጨረሻ ምርመራ የሚሆነው መኪናውን በከፍተኛ ፍጥነት መሞከር ነው - ጭነት ጭኖና ሳይጭን፡፡ ለምሳሌ አምስት ሰዎች የምትጭነውን ትንሿን መኪና ብንወስድ፣ ሾፌሩ ብቻውን እየነዳ ሲሄድ ምንም ችግር ላይኖር ይችላል፡፡ ከዚያም አራት ሰዎች ጭኖ ይሄዳል። በዚህ ጊዜ የተለያዩ ድምፆች የሚያሰሙ ከሆነ፣ እንደገና ይስተካከላል፡፡ ስለዚህ፣ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻ ድረስ ድርድር የሌለው የኳሊቲ ኮንትሮል ፍተሻና ቁጥጥር ስለሚደረግ የመኪኖቻችን የጥራት ደረጃ ከፍተኛ ነው” በማለት አቶ ቢኒያም አስረድቷል፡፡

በመገጣጠሚያው ውስጥ በአመራር ደረጃ ያሉ ሠራተኞች በኦቶሞቲቭና በኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው፡፡ የተቀሩት ደግሞ ከቴክኒክና ሙያ የተመረቁ ናቸው፡፡ ድርጅቱ ትጉህ ሠራተኞችን ወደ ቻይና ልኮ ያሠለጥናል፤ ከቻይና ባለሙያዎችን አስመጥቶም የሥራ ላይ ሥልጠና ይሰጣል፤ ጥሩ የሥራ ውጤት ያላቸውን ሠራተኞች በኮሚቴ ታይቶ ትምህርታቸውን እንዲያሻሽሉ የገንዘብ ድጋፍ ይደረግላቸዋል፡፡ በሌሎች መገጣጠሚያዎች የሠሩ ልምድ ያላቸው ሠራተኞችም አሉ፡፡

መገጣጠሚያው፣ ግንባታውና የማሽን ተከላው ተጠናቆ ሥራ የጀመረው በመስከረም 2003 ዓ.ም ነው፡፡ በመገጣጠሚያው ውስጥ ብቻ የሚሠሩ 65 ሠራተኞች ሲኖሩ፣ የሕክምናና የትራንስፖርት አገልግሎት ያገኛሉ፡፡ ያኔ ካፒታሉ 60 ሚሊዮን ብር እንደነበር አቶ ቢኒያም ገልጿል፡፡

የከባድ መኪና መገጣጠሚያ መስመር የተጠናቀቀ ሲሆን በተለያዩ ምክንያቶች ግን መገጣጠም አልጀመረም፡፡ ምን ዓይነት ተሽከርካሪ እንገጣጥም? ስንት ሰው የመጫን አቅም ያለው (28 ሰው፣ 48 ሰው፣ 65 ሰው፣ …) አውቶቡስ እንሥራ በማለት እያጠኑ ነው፡፡

ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ ፍቃዱም ሆኑ አቶ ቢኒያም፣ ጉምሩክ የሚያስከፍላቸው ቀረጥ ከፍተኛ በመሆኑ የሚያበረታታ እንዳልሆነ ይናገራሉ፡፡ አቶ ቢኒያም የቀረጥ ማበረታቻው አነስተኛ ነው ይላል። “ማንኛውም መኪና አስመጪ ከሚከፍለው ያላነሰ ነው የምንጠየቀው፡፡ እኛ እዚህ ለዜጐች የሥራ

ዕድል ፈጥረን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር አምጥተን፣ እሴት ጨምረን መሸጣችን፣ ምንም አልታሰበም፡፡ መርካቶ ሱቅ ተከራይቶ መኪና እያመጣ ከሚሸጠው እኩል ነው የምንቀረጠው፡፡ ይህ አሠራር ተወዳዳሪ ሆኖ መቀጠል ስለማያስችለን የቀረጥ አስተያየት እንዲደረግልን ጥያቄ አቅርበን እየተጠባበቅን ነው” ብሏል፡፡

በጉምሩክ አካባቢ እስካሁን ምንም ችግር አልገጠመንም ነበር ያሉት ሥራ አስኪያጁ፤ በቅርቡ በወጡ አዋጆች ላይ የአተረጓጐምና የአፈጻጸም (ደብል ታክሴሽን) ችግር መኖሩን ገልፀዋል፡፡

“ይኼ አሠራር ችግር አለው ብለን አመልክተናል፤ በጐ ምላሽም እንደምናገኝ እንጠብቃለን፡፡ ነገር ግን አሠራሩ አይሻሻልም፤ ይኸው ነው ከተባለ፣ መኪና አገር ውስጥ ከመገጣጠም ይልቅ ከውጭ አምጥቶ የሚከፈለው ታክስ ይመረጣል፡፡ ደብል ታክሴሽን የሚፀና ከሆነ፣ በፊት የሚከፈለውን እጥፍ ያደርገዋል፡፡ ይህ ደግሞ ኢንዱስትሪውንም ይገድላል” ብለዋል፡፡ ሌላው አቶ ፍቃዱ ያነሱት ችግር፣ ከፋይናንስ ተቋማት በሚፈለገው መጠን የገንዘብ ብድር ከማግኘት ነው፡፡

በላይአብ ሞተርስ፣ በቀን 18 መኪና የመገጣጠም አቅም አለው፡፡ አሁን ግን በሙሉ አቅሙ ማምረት ደረጃ አልደረሰም፡፡ የመስክ ፒክአፑን ለመገጣጠም 2፡30፣ የቤት መኪናዋን ለመገጣጠም ደግሞ 2፡00 ይወስድበታል፡፡ መኪኖቹን የሚገጣጥሙት መጋዘን ባለ ዕቃ ስለሆነ ብዙ ጊዜ ሽያጩ እጅ በእጅ ነው። ገዢው ክፍያውን ሲፈጽም ወዲያውኑ መኪናውን ይረከባል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ሽያጭ በርክቶ ከመጋዘን ዕቃ ሲያልቅና የታዘዘው እስኪመጣ ድረስ ብቻ ቀጠሮ እንደሚሰጡና ቅድምያ ክፍያ እንደማይጠይቁ አቶ ቢኒያም ተናግሯል፡፡

“ብዙ ጊዜ ገንዘብ ተቀብለን ቀጠሮ አንሰጥም። በዚህም ደንበኞች ይመርጡናል፡፡ ሌላው ጥሩ ነገር ደግሞ 6ሺህ የቀለም ዓይነት መያዛችን ነው፡፡ ሰዎች የተለያየ የቀለም ምርጫ ስላላቸው፣ መኪናው ቀለም ከመቀባቱ በፊት፣ ደንበኞች የፈለጉትን የቀለም ዓይነት እንዲመርጡ ዕድል እንሰጣቸዋለን። ድርጅቱ ከሚቀባቸው አምስት ቀለሞች ውጭ ደንበኛው የመረጠውን፣ ለመቀባት የአንድ ሳምንት ቀጠሮ እንሰጣለን፡፡ ይህም ተመራጭ አድርጐናል” በማለት አብራርቷል፡፡

ድርጅቱ፤ ከቀረጥ ነፃ መኪና እንዲያስገቡ ለተፈቀደላቸው ድርጅቶችም አገልግሎት ይሰጣል። “እኛ የመኪና አካላትን የምናስገባው ቀረጥ ከፍለን ነው፡፡ ከቀረጥ ነፃ ፈቃድ ያላቸው ድርጅቶች፣ የመኪኖቹ አካላት አገር ውስጥ ከመግባታቸው

በፊት ማዘዝ አለባቸው፡፡ እኛም ፈቃዱን አሳይተን ‘እነዚህን መኪኖች የምናስገባው ከቀረጥ ነፃ ነው’ ብለን ቀረጡን ማስቀረት እንችላለን” ብሏል አቶ ቢኒያም፡፡

ከበላይአብ ሞተርስ በፊት መኪና መገጣጠምና ሪልእስቴት የጀመሩ ድርጅቶች የገቡትን ቃል ሳያከብሩ ከአገር በመውጣታቸው መኪና ለመግዛትና ቤት ለማሠራት ገንዘብ የከፈሉ ሰዎች ችግር ውስጥ ወድቀዋል፡፡ በዚህ ድርጅት አስቀድሞ ገንዘብ መክፈል ባይኖርም፣ አንዳንድ ሰዎች “መኪና ገዝቻቸው ካገር ቢጠፉ መለዋወጫ አላገኝም” የሚል ስጋት ሊያድርበት ይችላል፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ችግር ምን ምላሽ ይኖራቸው ይሆን?

“የመለዋወጫ ችግር እንዳለ ጥናት አድርገን ስለነበር፣ መኪኖችን ከመገጣጠማችን በፊት የተለያዩ የመኪና አካላትና መለዋወጫቸውን አንድ ላይ ስላዘዝን ከእኛ መኪና የገዙ ደንበኞች አንዳችም ችግር አልገጠማቸውም፡፡ ለምንሸጣቸው መኪኖች የሁለት ዓመት ወይም የ40 ሺህ ኪ.ሜ ዋስትና እንሰጣለን፡፡ ኅብረተሰቡ በዚህ ዘርፍ በተፈጠረው ችግር የተነሳ፣ በተለያዩ ጊዜያት ስጋታቸውን ሲገልጹ ሰምተናል፡፡ ይሁን እንጂ እያንዳንዱ ድርጅት ያለው አቅም ምንድነው ብሎ መገምገም ተገቢ ነው፡፡ ከዚህ ኢንቨስትመንት ሌላ ምን አለው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም አንድ ኢንቨስትመንት ብቻ ከሆነ ዘግቶ ሊሄድ ይችላልና ነው፡፡

“በላይአብ ሞተርስ ከእርሻ እስከ ማኒፋክቸሪንግና ሆቴል ኢንዱስትሪ የተሠማራ ድርጅት ነው፡፡ በላይአብ አንድ ነገር ሠርቶ አላቆመም፤ በማስፋፋት ላይ ነው ያለው፡፡ ከዚህ ፋብሪካ ጐን በ50ሺህ ካሜ ቦታ ላይ ትልቅ የኬብል ማኑፋክቸሪንግ እየሰራ ነው፡፡ ቦሌ አካባቢ ባለ 5 ኮከብ ሆቴል እየተገነባ ሲሆን በዚህ ዓመት ይመረቃል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡ ፓዌ ላይ የእርሻ ልማት፣ በአዳማ ደግሞ የዶሮ እርባታ አለው፡፡ ኒኮን የተባለ የኮንስትራክሽን ድርጅትም ከፍተናል፡፡ ሌሎች ሊሠሩ የታቀዱና በጥናት ላይ የሚገኙም ፕሮጀክቶችም አሉ፡፡ እነዚህ ሁሉ የበላይአብን አቅምና ለአገር ልማት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ያሳያሉ፡፡ መኪኖቻችንን ለሰው በዱቤ ስንሰጥ የእኛ ገንዘብ ሰው ጋ አለ እንጂ እኛ ጋ የሰው ገንዘብ የለብንም፡፡ ገንዘባችንን በትነን የት ነው የምንሄደው? ስለዚህ በላይአብ እምነት የሚጥሉበት እንጂ አገር ጥሎ በመጥፋት የሚጠረጠር ድርጅት አይደለም” በማለት አቶ ቢኒያም ድርጅቱ ያለበትን ደረጃ አብራርቷል፡፡

አቶ መስፍን ብዙነህ፣ የድህረ ሽያጭ ጥገና አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ናቸው፡፡ ቃሊቲ

በሚገኘው የተንጣለለ የድርጅቱ ዎርክሾፕ በዋነኛነት የሚሰጠው አገልግሎት ድርጅቱ ለሸጣቸው ተሽከርካሪዎች ነበር፡፡ አሁን ግን ወደ ድርጅቱ ለመጣ ማንኛውም ተሽከርካሪ የጥገናና የሰርቪስ አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡

የመለዋወጫ ግብይት፣ የመጫንና የማውረድ አገልግሎት እንደሚሰጡም አቶ መስፍን ገልፀዋል። ከሚገጣጥሟቸው መኪኖች በተጨማሪ፣ ፉቶን ዳምትራክ፣ ፉቶን ፒክአፕ በብቸኝነት የሚያስመጣው በላይአብ ነው፡፡ ሲኖ ዳም ትራክም፣ ያስመጣሉ፡፡ ከከባድ መሳሪያ ደግሞ ሎደርና ግሬደር በኮንቴይነር አስመጥተው በወርክሾፑ ይገጣጥማሉ፣ የሰርቪስና የጥገና አገልግሎት እንደሚሠጡም ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡

የበላይአብ የወደፊት ዕቅድ የሚገጣጥማቸውን መኪኖች ለምሥራቅ አፍሪካ ገበያ በማቅረብ ለአገሩ የውጭ ምንዛሪ ማስገኘት ነው፡፡ “ይህን ለማድረግ ኅብረተሰቡና ደንበኞቻችን በሚገባ ሊያውቁን ይገባል፡፡ በአንድ ወይም በጥቂት ድርጅቶች የተፈጠረ ጥፋት፣ በሁሉም ድርጅቶች ይፈጠራል ብሎ ማሰብ አይገባም፡፡ ሌላው ደግሞ ሰዎች አመለካከታቸውን መለወጥ አለባቸው፡፡

“የሚያወዳድሩትን ነገር ወይም ድርጅት በትክክለኛ መመዘኛ ማወዳደር አለባቸው፡፡ አንድም ኪ.ሜ ያልተነዳ፣ ጌጁ (ኪ.ሜ ቆጣሪው) ዜሮ ላይ ያለ አዲስ መኪናና ከ25 ዓመት በፊት ተመርቶ በየበረሃው ጨው የበላውን መኪና ከመግዛት በፊት ቆም ብሎ በማሰብ እውነታውን መረዳት ያስፈልጋል። እውነቱን ሳይለዩ በአሉባልታ መመራት በጣም መጥፎ ባህርይ ነው፡፡

ነገሮችን የማጥላላት ባህርይ ያለው ሰው “መጥፎ ነው” ያለውን ከመቀበል፣ የእኛን መኪኖች የገዙ ሰዎችን በማነጋገር ስለመኪኖቹ ትክክለኛ መረጃ ማግኘት ይበጃል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ገበያው ሁሉ በአሉባልታ የተሞላ ይሆናል፡፡ ችግሮች እንኳ ቢኖሩ ከአገር አኳያ ማየትና ችግሩን በመነጋገር መፍታት ነው የሚሻለው። ድርጅቱ ዛሬ ባያተርፍ ለመጪው ትውልድ መነሻ ትተን ነው የምናልፈው፡፡ ከዚህ አንፃር ነው መታየት ያለበት” በማለት የመገጣጠሚያው ፋብሪካ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢኒያም መልዕክት አስተላልፏል፡፡

የበላይአብ ሞተርስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍቃዱ ግርማ ደግሞ በቀጣዩ ዓመት የሥራ አድማሳቸውን በማስፋት የሚገጣጥሟቸውን ተሽከርካሪዎች ወደጐረቤት አገሮች ለመላክ፣ በሀገር ውስጥም፣ አካባቢን የማይበክሉ አዳዲስ ሞዴል ተሽከርካሪዎችን ለማቅረብ ማቀዳቸውን ገልፀዋል፡፡

Page 26: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 26

ፀሐይ ተፈረደኝ (ከኢሶግ)

ላንቺና ላንተ

ይህንን አምድ አዘጋጅቶ የሚያቀርብላችሁ ESOG-Ethiopian Society of Obstetricians and Gynecologists (የኢትዮዽያ የፅንስና የማህፀን ሀኪሞች ማኅበር) ነው፡፡ (በፖ.ሣ.ቁ 8731 ስልክ 011-5-506068/69 ልታገኙን ትችላላችሁ)

እ.ኤ.አ 2013 ዓ/ም ወደ ማለቂያው እየተዳረሰ ነው፡፡ የዛሬ አስራ ሶስት አመት ማለትም እ.ኤ.አ በ2000/ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሀገራትን አስተባብሮ አለም አቀፍ የልማት ግቦችን መንደፉ ይታወሳል፡፡ 189/ የተባበሩት መንግስታት አባል ሀገራት በጋራ ወደ ስምንት የሚደርሱ የልማት ግቦችን ከነበሩበት ደረጃ እስከ 2015/ዓ/ም መሻሻል እንዲያሳዩ ሲታቀድ በዚ ህም ወደ 23/ የሚደርሱ አለም አቀፍ ድርጅቶች ግቡ እንዲሳካ ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ በት መድረክ ይታወሳል፡፡ ከእነዚህ ስምንት የልማት ግቦች ውስጥ የተወሰኑት ከጤና ጋር የተ ያያዙ ናቸው፡፡ በቅርቡ በተሰማው ዜና የልማት ግቦቹን ከማሳካት አንጻር በተለይም በአፍሪካ ወደ አምስት ሀገሮች በአብዛኛው የተሳካላቸው መሆኑ እና ኢትዮጵያ እንዲያውም ቀዳሚውን ስፍራ እንደያዘች ተገልጾአል፡፡ በኢትዮጵያ በተለይም ከሕጻናት ሞት ጋር የተያያ ዘው የልማት ግብ የተሳካ መሆኑ ቀደም ብሎ ተገልጾአል፡፡ ነገር ግን ከእናቶች ጤና ጋር በተያዘ የታለመወ ግብ እስከአሁን ድረስ ከተጠበቀበት ያልደረሰ በመሆኑ ወደፊት በተወሰነለት ጊዜ ከግቡ መድረስ ይችላልን? ከሚል ለሚሰነዘሩ ጥያቄዎች በኢፊድሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ቸውን ሰጥተዋል፡፡

-----///------ጥ/ የምእተ አመቱ የልማት ግብ ከጤና አኩዋያ ከምን

ደረጃ ላይ ይገኛል ? መ/ ከምእተ አመቱ የልማት ግቦች መካከል ቁጥር 4 ፣5 እና

6 / በቀጥታ ከጤና ጋር የተገናኙ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ በተራ ቁጥር 4/ የተመዘገበው የህጻናትን ሞት መቀነስ የሚባለውን በተባበሩት መንግስታት እንደተረጋገጠው ኢትዮጵያ በ2012ዓ/ም አሳክታለች፡፡ በ6ኛው ተራ ቁጥር የተመዘገበው የልማት ግብ ተላላፊ በሽታዎችን ፣ ሳምባን ፣ወባንና ኤችአይቪን መቀነስ ሲሆን ይህንንም ኢትዮጵያ በልማት ግቡ እቅድ መሰረት ካሳኩት አገራት መካከል ተመድባለች፡፡ ነገር ግን ትልቁ ችግር በተራ ቁጥር 5/ የተመዘገበው ከእናቶች ጤና ጋር የተያያዘው የልማት ግብ ምንም እንኩዋን እስከአሁንም ብዙ የተሰሩ ስራዎች ቢኖሩም ከተፈለገው ደረጃ ግን አልተደረሰም፡፡ ስለዚህም ክፍተት ስለሚታይ ገና ብዙ መስራት እንደሚጠበቅብን ግልጽ ነው፡፡

ጥ/ የምእተ አመቱን ቁጥር 5 /የልማት ግብ ለማሳካት በኢፊድሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስር ምን በመደረግ ላይ ነው?

መ/ የእናቶች ሞት ከሚመጣባቸው ምክንያቶች መካከል ሶስቱ መዘግየቶች የሚባሉት ትልቅ ችግር እንደሆኑ ይታወቃል፡፡

የመጀመሪያው መዘግየት እናቶች ከመውለዳቸውም በፊት

የእናቶች ሞት በኢትዮጵያ በየአመቱ 4.9 % ያህል እየቀነሰ ነው ሆነ ከወለዱ በሁዋላ ወደ ጤና ተቋም ሄደው ከሕክምና ባለሙያ ጋር ምክር አለማድረጋቸው እና በወሊድ ጊዜ በጤና ተቋም ሄደው አለመው ለዳቸው ነው፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ የቤተሰብ የልማድ፣ የባህል የመሳሰለው የአመለካከት ችግር ወደጤና ተቋም ሄደው እንዳይወልዱ ማድረግ አንዱ ተጠቃሽ ችግር ነው፡፡ ይህንን ችግር ለመፍታት በጤና ጥበቃ ሚኒስር የጤና የልማት ሰራዊት የሚባል በአገር ደረጃ ኃይል የተደራጀ ሲሆን አንድ ለአምስት በሆነ አሰራር እናቶችን፣ ቤተሰቡን የሚመለ ከተውን ሁሉ በሚያዳርስ መልክ እንዲሁም የልማት ቡድን በማዋቀር ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ የዚህ ስራ ዋና አላማው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በተለይም እናቶችን በማነቃቃት የአመለካከትን ችግር ለመለወጥ ነው፡፡ ይህም በተግባር እየተተረጎመ ነው፡፡

ሁለተኛው መዘግየት የሚባለው እናቶች ወደ ሆስፒታል መሄድ እየፈለጉ በትራንስፖርት ችግር ምክንያት መቅረታቸው ነው፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስር ይህንን ችግር ለመፍታት በሁለት መንገድ እየተከታተለው ነው፡፡

እናቶችን ወደ ጤና ተቋም ለማድረስ እስከዋና መንገድ ድረስ ማለትም መኪና ሊገባበት እስከሚችለው መንገድ ድረስ ባህላዊ አምቡላንሶችን በአካባቢው ቁሳቁስ እንዲዘጋጁ በማድረግ በአካባቢው በሚኖሩ ወጣቶች አማካኝነት በማጉዋጉዋዝ ላይ ስንሆን በዚህም ትልቅ ለውጥ እየታየ ነው፡፡

እናቶች በባህላዊ አምቡላንስ አማካኝነት ወደ ዋና መንገድ ከደረሱ በሁዋላ ደግሞ አምቡላንስ በማቅረብ ወደጤና ተቋም እንዲደርሱ እየተደረገ ነው፡፡ ጤና ጥበቃ ሚኒስር በወረዳ ደረጃ አንድ አምቡላንስ ... ባጠቃላይም ወደ ስምንት መቶ አምቡላንሶችን አሰማርቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው። የአንቡላንሶቹን አቅርቦት በተለይም ሰፋፊ ወረዳዎች ላይ ቁጥራ ቸውን ለመጨመር እንዲቻል አሁንም ወደ አራት መቶ አምቡላንሶች የተ ዘጋጁ ሲሆን በቅርቡ ለተገልጋዩ ይቀርባሉ። ስለዚህ ሁለተኛውን መዘግየት በዚህ መንገድ ለመቅረፍ ስራ በመሰራት ላይ ነው፡፡

ሶስተኛው መዘግየት የሚባለው እናቶች ጤና ተቋም ከደረሱ በሁዋላ በጤና ተቋም አማካኝነት የሚደርሱባቸው ችግሮች ናቸው፡፡ ይኼውም የሚገለጸው ፡-

የጤና ተቋማቱ ለእናቶች በቅርበት አለመኖራቸው፣እናቶች የሚፈልጉትን አገልግሎት በተገቢው ሁኔታ

አለማቅረብ፣ የሚሉት በሶስተኛው መዘግየት የሚጠቀሱ ናቸው።

ይህንንም ለመቅረፍ በኢትዮጵያ በመጀመሪያ ደረጃ ጤና

አገልግሎት ከ3200 ሶስት ሺህ ሁለት መቶ በላይ ጤና ጣቢያ ዎች እና ከ 17000 አስራ ሰባት ሺህ በላይ ጤና ኬላዎች እንዲሁም 126 አንድ መቶ ሀያ ስድስት የገጠር ሆስፒታል በስራላይ ያሉ ሲሆን በተጨማሪም 150 አንድ መቶ ሀምሳ በዚህ አመት ወደስራ ይገባሉ፡፡ ስለዚህ አጠቃላይ ያለውን ሽፋን ከ95% ማድረስ ተችሎአል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተለያዩ የህክምና መሳሪያዎችን በመድሀኒትና አቅርቦት ፈንድ ተቋም ለማቅረብ ተችሎአል፡፡

ጥ/ የእናቶችን ሞት ለመቀነስ በከፍተኛ ሁኔታ መሰራት ይገባዋል የሚባለው የትኛው ነው?

መ/ የእናቶችን ሞት ለመቀነስ በከፍተኛ ሁኔታ መሰራት አለበት የሚባለው የጤና ባለሙያዎችን በሚመለከት ነው፡፡ የጤና ባለሙያዎች ሲባልም ሐኪሞች ፣ነርሶች ፣ሚድ ዋይፎች ፣ኼልዝ ኦፊሰሮች ፣የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስቶች ያስፈልጋሉ፡፡ ይህንን የባለሙያ እጥረት ለመቅረፍ በሕክምናው ዘርፍ የተወሰኑ አመታትን ከሰሩ በሁዋላ ለማስተማር ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲዎችም የቅበላ አቅማቸውን በመጨመር ትምህርቱን በማስተማር ላይ በመሆናቸው አበረታች ሁኔታ እየታየ ነው፡፡ ነገር ግን አንድን ጠቅላላ ሐኪም የጽንስና ማህጸን ሐኪም ለማድረግ አራት አመት ይፈጃል፡፡ ስለሆነም ለምእተአመቱ የልማት ግብ ውጤታማነት ለመድረስ አዳጋች ስለሚሆን የጤና ጥበቃ ሚኒስር እንደ ኢሶግ ካሉ አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ባለሙያዎች አቅማቸውን እንዲያደረጁ በማድረግ ላይ ነው፡፡ በዚህ አሰራርም የጤና መኮንኖችን ሶስት አመት በማሰልጠን በአፋጣኝ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ስራ ላይ እንዲሰማሩ ለማድረግ ገጠር ላሉ ጤና ተቋማት ለእያንዳንዱ ሁለት ሁለት ለማዳረስ በማሰብ አንድሺህ ባለሙ ያዎችን ለማሰልጠን ሁኔታዎች እየተመቻቹ ነው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ሁለት መቶ የሚሆ ኑት ስልጠናቸውን ጨርሰው ወደ የሆስፒታሉ የተመደቡ ሲሆን ከዚያም በላይ ይጠበ ቃል፡፡ አንድ የጤና ባለሙያ ቀዶ ሕክምና በሚያካሂድበት ጊዜ ስራውን ብቻውን ስለማይሰራው አዋላጅ ነርሶች እንዲሁም ሰመመን ሰጪዎችም አብ ረው ስልጠናውን እየወሰዱ ነው፡፡ ስለዚህ ሙያው እጅ ለእጅ በመያያዝ መልክ ከግንዛቤ ማስጨበጥ እስከጤና ባለሙያ ማፍራት ድረስ በመሰራት ላይ በመሆኑ የእና ቶችን ሞት ለመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል፡፡

የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይርጉ ገ/ሕይወት በምእተ አመቱ የልማት ግብ በተለይም በተራ ቁጥር 5/የተመዘገበው የእናቶች ሞትን መቀነስ

በሚመለከት በሰጡት አስተያየት፡- “… በእርግጥ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ ነው፡፡ ነገር ግን

የሚሰሩት ስራዎች በአፋጣኝ ውጤት የሚገኝባቸው ላይሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን የተሰሩ ስራዎች ነገ ተነገወዲያ ጥሩ ውጤት እንደሚያሳዩ እሙን ነው፡፡ የእናቶችን ሞት ከሶስቱ መዘግየቶች ጋር ብቻ አያ ያዘን የምእተ አመቱን ግብ አልተሳካም ብለን መደምደም የለብንም፡፡ ምክንያቱም እናቶ ችን ከማዳን አንጻር ሌሎች ብዙ የሚጠቀሱ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ ኤችአይቪ ኤይድስ ለእናቶች ሞት ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ምክንያት ሲሆን በዚህ ላይ ብዙ ጥሩ ነገር ተሰ ርቶአል፡፡ ወባ ለእናቶች ሞት ምክንያት እንደሚሆን እርግጥ ሲሆን የወባ መቀነስ ለእና ቶች ጤንነት መሻሻል አንዱ ምክንያት ነው፡፡ በቤተሰብ እቅድ አገልግሎት በኩል ከፍተኛ ስራ እየተሰራ በመሆኑ ወደ አምስት እጥፍ ያህል ሽፋኑ ጨምሮአል፡፡ ይህም የእናቶችን ጤና ለማሻሻል አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ምንም አያጠያይቅም፡፡ የተባበሩት መንግስታት ጥናት እንደሚያሳየው የእናቶችን ሞት በመቀነስ ረገድ በኢት ዮጵያ ባለፉት ሀያ አመት ውስጥ በየአመቱ 4.9 ኀ ያህል እየቀነሰ መሆኑን ያሳያል፡፡ይህ ውጤት የሚያሳየን የል ማት ግቡን በጊዜው ልናሳካ ባንችልም እንኩዋን ጥሩ ውጤት መሆኑን መገንዘብ ይገባ ናል...ብለዋል፡፡”

ዶ/ር አሚር አማን

የእርሻና የፋብሪካ ምርቶች፣ በጥራትና በብዛት እየቀረቡ አይደለም በማለት የተናገሩት የንግድ ሚኒስቴር ሃላፊዎች፣ “ትልልቅ ፕሮጀክቶች በውጭ ምንዛሬ እጥረት እየተቀየዱ የሚሄዱበት እድል ሰፊ ነው” በማለት አሳሳቢነቱን ገልፀዋል።

ከአመት አመት የኤክስፖርት እድገት እየተዳከመ መምጣቱን የሚክድ ይኖራል ብዬ አልገምትም። አሁን ደግሞ፣ ከነጭራሹ ቅንጣት እድገት አልታየም። እንዲያውም የኤክስፖርት ገቢ ቀንሷል። በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ውስጥ ከተዘረዘሩት “ግቦች” ጋር ሲነፃፀርማ፣ በእጅጉ ወደኋላ ቀርቷል። የእቅዱ ግማሽ ያህል እንኳ አልተሳካም።

በእቅዱ የመጀመሪያ ዓመት በ2003 ዓ.ም፣ ሁለት ቢሊዮን ዶላር የነበረውን የኤክስፖርት ገቢ በአንድ ቢሊዮን ዶላር ለማሳደግ (3 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ) ቢታሰብም፣ የእቅዱ 75 በመቶ ብቻ ነው የተሳካው። ቀላል እድገት ነው ማለቴ አይደለም። 2.75 ቢሊዮን ደርሷል። በቀጣዩ ዓመት ግን፣ እድገቱ ተዳክሟል። በ“ኦሪጅናሉ” እቅድ መሰረት፣ የኤክስፖርት ገቢ በ2004 ዓ.ም ወደ አራት ቢሊዮን ዶለር የሚጠጋ ይሆናል ተብሎ ነበር የታሰበው። በተግባር የተገኘው ገቢ ግን 3.15 ቢ. ዶላር ነው። ከመነሻው አመት ጋር ሲነፃፀር በሁለት ቢሊዮን ዶላር የሚበልጥ ገቢ ለማግኘት ቢታቀድም፣ በተግባር የተገኘው እድገት 1.2 ዶላር ገደማ ነው። እናም እቅዱ 60 በመቶ ብቻ ነው የተሳካው ማለት ይቻላል።

አሁንም ኦሪጅናሉን እቅድ ካስታወስን፣ በ2005 ዓ.ም ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ የኤክስፖርት ገቢ ለማግኘት ታስቦ እንደነበር እናያለን። በተግባር የተገኘው ውጤት ደግሞ 3.1 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። የአመት አመት እድገቱ ተዳክሞ ከመቆሙም በላይ፣ የኋሊት መንሸራተት ጀምሯል። በ2002 ዓ.ም ከነበረው መነሻ አሃዝ ጋር ስናነፃፅረው፣ በሦስት ቢሊዮን ዶላር የላቀ እንዲሆን ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ 1.1 ቢሊዮን ዶላር ያህል ብቻ ነው የተሳካው። የእቅዱ 37% ብቻ ማለት ነው። ከአመት አመት የስኬቱ መጠን እየቀነሰ መሆኑን የምታስተውሉ ይመስለኛል።

ዘንድሮም የኤክስፖርት ገቢ ከሰባት ቢሊዮን ዶላር የሚበልጥ ይሆናል ተብሎ በእድገትና

ትራንስፎርሜሽ እቅዱ ውስጥ ተጠቅሷል። ሃሙስ እለት የወጣው የአይኤምኤፍ መግለጫ እንደሚያመለክተው ግን፣ የኤክስፖርት ገቢው 3.6 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ይሆናል ተብሎ ነው የሚጠበቀው።

እንግዲህ አስቡት፤ የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅዱ ላይ የሰፈረው፣ በ2002 ዓ.ም ሁለት ቢሊዮን ዶላር የነበረውን የኤክስፖርት ገቢ፣ በ2006 ዓ.ም በአምስት ቢሊዮን ዶላር ይጨምራል የሚል እቅድ ነው። በእውን ይታያል ተብሎ የሚጠበቀው ጭማሪ ግን 1.5 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። የእቅዱ 33% ብቻ መሆኑ ነው።

የእቅዱ ስኬት ከአመት አመት እየቀነሰና እየተሸረሸረ የመጣው አለምክንያት አይደለም። የእቅዱ መዘዝ ከአመት አመት እየጨመረና እየተደራረበ ስመጣ ነው። ‘መዘዝ’ ስል፣ ያልታሰበና ያልተጠበቀ መመዝ ማለቴ አይደለም። በደንብ ታስቦበታል። ከዚያም አልፎ፣ የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ ላይ በይፋ ተዘርዝሯል። በአምስት አመታት ውስጥ በአገሪቱ ከሚካሄዱ የኢንቨስትመንት ስራዎች ውስጥ 67 በመቶ ያህሉ በመንግስት ፕሮጀክቶች፣ 33 በመቶ ያህሉ ደግሞ በግል ኢንቨስትመንት እንደሚሸፈን በ“እቅዱ” ውስጥ ተጠቅሷል። በሌላ አነጋገር፣ የመንግስት ፕሮጀክቶች፣ ከግል ኢንቨስትመንቶች በእጥፍ እንዲበልጡ ነው የታቀደው።

ድሮ እንደዚያ አልነበረም። ኢህአዴግ ስልጣን በያዘባቸው የመጀመሪያ አመታት፣ ከመንግስት ፕሮጀክቶች ይልቅ የግል ኢንቨስትመንት ድርሻ ይበልጥ ነበር - (የግል ኢንቨስትመንት 70 በመቶ የመንግስት ደግሞ 30 በመቶ)። መንግስት የነፃ ገበያ ኢኮኖሚን እገነባለሁ ቢልም፣ ቀስ በቀስ የግል ኢንቨስትመንት ድርሻ እየቀነሰ፣ በተቃራኒው የመንግስት ፕሮጀክቶች ድርሻ እየጨመረ መጥቷል። የዛሬ አስር አመት ገደማ ነው፣ የሁለቱ ድርሻ እኩል የሆነው (ሃምሳ በመቶ - ሃምሳ በመቶ)። የዚህን ጊዜም ነው፣ በመላው ዓለም ወደ ሶሻሊዝም ያዘነበሉ ናቸው ከሚባሉ አምሳ አገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗ የተገለፀው።

የቁልቁለት ጉዞው ግን በዚሁ አላቆመም። አይኤምኤፍ ሀሙስ እለት ባሰራጨው ዘገባ

እንደገለፀው፣ የግል ኢንቨስትመንት ድርሻ ወደ 25 በመቶ እንደወረደና የመንግስት ፕሮጀክቶች ድርሻ 75 በመቶ እንደደረሰ ይገልፃል። በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ውስጥ ከተጠቀሰውም በላይ የከፋ መሆኑን ተመልከቱ። እንዲህ አይነት የመንግስት ገናናነት፣ በብዙ አገራት ውስጥ የለም። በእጅጉ ሶሻሊስታዊ የኢኮኖሚ አካሄድን ከሚከተሉ ሶስት የዓለማችን አገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ ሆናለች የተባለውም በዚህ ምክንያት ነው። ነፃ ገበያ እንዲህ ነው እንዴ?

የመንግስት ፕሮጀክቶች ድርሻ እያበጠ፣ የግል ኢንቨስትመንት ድርሻ እየተደፈጠጠና እየቀጨጨ የመጣው፣ በተለያዩ ምክንያቶች ቢሆንም፣ ትልቁና ዋናው ሰበብ ግን ከባንክ ብድር ጋር የተያያዘ ነው። የባንክ ብድሮች ከአመት አመት ከግል ኢንቨስትመንት እየራቁ ወደ መንግስት ፕሮጀክቶች እንዲጎርፉ ተደርጓል። ከ20 አመታት በፊት፣ ከግማሽ በላይ የባንክ ብድሮች ለግል ኢንቨስትመንትና ለግል ቢዝነሶች የሚውሉ ነበሩ።

ግን ብዙም ሳይቆይ የባንክ ብድር አቅጣጫው ተቀይሮ፣ ወደ መንግስት ድርጅቶችና ፕሮጀክቶች መጉረፍ ጀመረ። በ2003 ዓ.ም፣ ከባንኮች አዲስ ብድር ውስጥ 70 በመቶ ያህሉ ለመንግስት ድርጅቶችና ፕሮጀክቶች እንደተሰጠ የሚገልፀው የአለም ባንክ ሪፖርት፣ ከዚያ ወዲህ ባሉ አመታትም የግል ድርጅቶች የሚያገኙት ብድር ይበልጥ እየቀነሰ እንደመጣ ያትታል። አሁን፣ ከባንኮች ብድር ውስጥ 90 በመቶ ያህሉን የሚወስዱት የመንግስት ድርጅቶችና ፕሮጀክቶች ናቸው። State Owned Enterprises are increasingly absorbing domestic banking sector credit. In the six-month period from June 2011 to December 2011, 71 percent of new loans were directed towards public enterprises. This share increased to 89 percent during the second half of 2012. A substantial share of the available foreign exchange is similarly diverted towards public investment. (የአለም ባንክ ሪፖርት Ethiopia Economic Update II፡ Laying the Foundation for Achieving Middle Income Status፡ June 2013 … ገፅ 24)

በዚህ መልኩ፣ ለግል ኢንቨስትመንት የሚውል የባንክ ብድር እየተንጠፈጠፈ፣ የግል ኢንቨስትመንት እየቀጨጨ ሲሄድ፣ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እየቀነሰ መምጣቱን ምኑ ይገርማል? ከሞላ ጎደል በሸቀጦች ኤክስፖርት የሚገኘው ገቢ፣ በግል ድርጅቶችና ኢንቨስትመንቶች አማካኝነት የሚመጣ ነዋ። ታዲያ፣ መንግስት ራሱን በራሱ ጠልፎ አልጣለም ትላላችሁ? በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ውስጥ የተዘረዘሩትን ትልልቅ ፕሮጀክቶች ለማከናወን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ያስፈልገዋል። ነገር ግን፣ “እቅዱ” ራሱ፣ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ የሆኑ የግል ኢንቨስትመንቶችን የሚደፈጥጥና የሚያቀጭጭ ነው።

ዜጐች ከገፅ 5 የዞረ

በደቡብ ክልሎች የስራ መደብ ተፈጥሮላቸው ተቀጥረው እየሠሩ ነው፤ በአዲስ አበባና በተቀሩት ክልሎች ግን እስካሁንም ለትምህርት መስኩ እውቅና ለመስጠት ማንገራገሮች አሉ” ብለዋል-አቶ ሲሳይ፡፡ በ2002 ዓ.ም የፌደራል ሲቪል ሠርቪስ ሚኒስቴር በሁሉም የክልል መስተዳድሮች በሚገኙ ወረዳዎች ሣይቀር በዚህ የትምህርት መስክ የተመረቁ ስራ ፈላጊዎች የሚሣተፉበት የስራ መደብ ተፈጥሮ ቅጥሮች እንዲከናወኑ የሚያዝ መመሪያ መተላለፉን ያስታወሡት አቶ ሲሣይ፤ መመሪያውን ተግባራዊ ለማድረግ ግን ቸልተኝነት መስተዋሉን ገልፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ የትምህርት ክፍሉ አሁንም ቢሆን ሠፊ የስራ እድል ያለው በመሆኑ አመለካከቱን ለመቀየርና ሁሉም ተመራቂዎች ስራ እንዲያገኙ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት ጋር በሠፊው እየተነጋገሩበት እንደሆነ አቶ ሲሣይ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

የትምህርት ክፍሉ በግለሰቦች በጐ ፈቃድ ነው የተከፈተው የሚባለው ግን አቶ ሲሳይ አይቀበሉትም፡፡ “ዲፓርትመንቱ በዩኒቨርስቲው የተከፈተው ህጋዊ ሆኖ ነው፤ መጀመሪያ የፍላጐት ጥናት (need assesment)፣ ከዚያም የተለያዩ ወርክሾፖች ተካሂደው ነው ወደ ስራ የተገባው” ሲሉም አስረድተዋል፡፡

ተመራቂዎች ከገፅ 2 የዞረ

Page 27: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 27 ስፖርት አድማስ

ግሩም ሠይፉ

አቶ ጁነዲን ባሻህ የኢትዮጵያን እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ለሚቀጥሉት አራት አመታት በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ የተመረጡት ዋልያዎቹ የዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ የመጀመርያ ጨዋታቸውን በአዲስ አበባ ከማድረጋቸው ሶስት ቀናት ቀደም ብሎ በተካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ነበር፡፡ የድሬደዋ ከተማ መስተዳድርን በመወከል በምርጫው ተወዳድረው ድምፅ ከሰጡት 106 የጠቅላላ ጉባዔ አባላት የ55ቱን ድምፅ በማግኘት አዲሱ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ሆነዋል፡፡ አቶ ጁነዲን ላለፉት 20 ዓመታት ከስፖርቱ ጋር ትስስር ነበራቸው፡፡ በተለይም የሐረር ቢራ ክለብ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነው በሰሩበት ወቅት ክለቡን ለፕሪሚየር ሊግ አብቅተውታል፡፡ ስለዓላማቸው በኢትዮጵያ እግር ኳስ አስተዳደር ግልፅነትና ተጠያቂነት ለማስፈን እሰራለሁ ብለዋል፡፡ በመላው አገሪቱ እግር ኳስን በተሻለ ደረጃ ለማስፋፋት ተስፋ እንደሚያደርጉ በመግለፅ፤ ስፖርቱን በተረጋጋ የለውጥ ሂደትና በዘመናዊ መዋቅር ለመምራት እንደሚፈልጉና በወጣት ፕሮጀክቶች ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል፡፡ በንግድና ኢንቨስትመንት ስራዎች ከፍተኛልምድ ያላቸው አቶ ጁነዲን ባሻህ እግር ኳስ ከዝንባሌ ባሻገር ትልቅ ንግድ እንደሚሆን በተግባር የማሳየት ፍላጎት እንዳላቸው ያስገነዝባሉ፡፡ ክለቦች የገቢ ምንጮቻቸውን በማስፋት ሊለወጡ በሚችሉበት የእድገት አቅጣጫ ላይ በጋራ ለመስራት ዝግጁ ናቸው፡፡ አቶ ጁነዲን ባሻህ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ሆነው በተሾሙበት እለት ከዚህ በታች የቀረበውን አጭር ቃለምምልስ ከስፖርት አድማስ ጋር አድርገው ነበር፡፡

በሃላፊነት ሳምንት እንኳን ሳይሞላዎት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ወደ ዓለም ዋንጫ ለማለፍ ወሳኝ የጥሎ ማለፍ ትንቅንቁን በሜዳው ይጀምራል፡፡ ሁኔታውን እንዴት ይመለከቱታል?

በአንድ በኩል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለአለም ዋንጫ ባያልፍ ምን ይመጣ ይሆን የሚለው ያስጨንቀኛል። እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ውጤት እንዲመጣ ከመጓጓት ነው። አሁን ደግሞ ሃላፊነት ላይ እንደተቀመጠ ሰው በዚህ ሽግግር የተጨናነቁ ነገሮች እንዳይመጡ ፍላጐቴ ነው፡፡ ቢቻል ከቀድሞው አመራር ጋር በቦታው ተገኝተን ቡድናችንን በጋራ ብናይ፣ በሰከነ ሁኔታ ተጨዋቾቻችን እንዲጫወቱ ፤ ተመልካቾችም ድጋፍ እንዲሰጡ አስባለሁ፡፡ በአጠቃላይ መልካም ነገር እመኛለሁ። ዋሊያዎቹ መልካም ነገር እያስመዘገቡ ነው የመጡት፡፡ አሁንም የምንጠበቀው ይህን ነው፡፡ የአመራር መለዋወጥ ከውጤቱ ጋር ብዙም የሚነካካ ነገር የለውም፡፡

ዋልያዎቹ ለዓለም ዋንጫ ቢያልፉ ለኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን ያመጣል፡፡ እርስዎ ምን ይጠብቃሉ?

በኢትዮጵያ የስፖርት ታሪክ ተመልካች ስታድዬም እየገባ በእግር ኳስ ውጤት እያዘነ የወጣበት ዓመታት ብዙ ናቸው፡፡ ለዚህ ተመልካችና ለዚህ ህዝብ ብሄራዊ ቡድኑ ለዓለም ዋንጫ ቢያልፍ መቼም ለሁላችን የሚፈጠረው ደስታ መጠን ያለው አይመስለኝም። እንግዲህ ይህን የሚፈጽሙት ሜዳ የሚገቡት ተጫዋቾች እና የብሄራዊ ቡድኑ አጠቃላይ አባላት ናቸው፡፡ አደራውን ለተጨዋቾችና ለአሠልጣኝ ነው የምሰጠው፡፡ በአጠቃላይ ለዓለም ዋንጫ ማለፍ በአፍሪካ እና ዓለም ደረጃ ጥሩ ገጽታ ይፈጥርልናል ብዬ ነው የማስበው፡፡

ድሮ ኳስ ስንት ቁጥር ለብሰው ነበር የሚጫወቱት?በተማሪነቴ ስምንት ቁጥር ለብሼ ነበር የምጫወተው፡፡ ከውጭ ኳስ የማን ጨዋታ ደስ ይልዎታል?የእንግሊዝ እና የስፔን ክለቦችን በብዛት እከታተላለሁ፡፡ የሚያደንቁት ተጫዋችስ?በፊት ለአርሰናል ይጫወት የነበረው ሄነሪ በጣም ደስ

ይለኝ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ የሮናልዶና የሜሲ አጨዋወት በጣም ይስበኛል፡፡

ዋልያ የሚለው ቅፅል ስም ተስማምትዎታል?በአገራችን ያለ ብርቅዬ እንስሳ ስለሆነ አዎ ለአለም ላይ

የቱሪዝም ሃብታችንን ማስተዋወቅ ነው፡፡ የድሬድዋ ሰው ኳስን የሚወደው በምን የተነሳ ነው?ድሬዳዋ ሜዳው ለጥ ያለ ነው፡፡ አሸዋ ነው፡፡ ብትወድቅም

ብትንከባለልም፡፡ የሚወስደን ጐርፉ ብቻ አይደለም፡፡ አሸዋውም ላይ ኳሱም አለ፡፡ ህዝቡ በተፈጥሮው ለፊልም፣ ለቲያትር በአጠቃላይ ለጥበብ የተሰጠ ነው፡፡ ባህሉ ሰውን የሚያቀራረብ ነው፡፡ ድሬደዋ ለጅቡቲ ካላት ቅርበት በብዙ መልኩ የአለምአቀፍ ዕሳቤ እና ስልጣኔ አላት፡፡ ስፖርት ደግሞ ስልጣኔ ነው፡፡ በስፖርቱ መስክ የሚመዘገብ እድገት እና ለውጥ የስልጣኔ መገለጫም ይሆናል፡፡

ወደ ስፖርት ከገቡ ከ20 ዓመታት በላይ አስቆጥረዋል። በእነዚህ ጊዜያት ብዙ አመራሮች በፌደሬሽኑ አስተዳደር ተቀያይረዋል፡፡ እርስዎ የፌደሬሽን አመራር እሆናለሁ ብለው አስበውት ያውቃሉ?

ስፖርት ያረካኝ ነበር፡፡ ስፖርትን ኳስ በመምታት አይደለም የማስበው ከዛ በላይ ነው፡፡ ክለብ ስናቋቁምም ወጣቱ የሚያተኩርበት ነገር እንዲያገኝ ከሚል ነው፡፡ አንዳንዴ ያሰብክበት ብቻ አይደለም የምትውለው ፈጣሪ የትም አውሎ ያስገባኝ የምትልበት ጊዜ አለ፡፡

ኢትዮጵያና ናይጄርያ ወደ ዓለም ዋንጫ ጥሎ ለማለፍ የገቡት ትንቅንቅ ከወር በኋላ በመልስ ጨዋታ ይለይለታል። ዋልያዎቹ በናይጄርያዋ ከተማ ካላባር በሚገኘው ዩጄ ኡሱዋኔ ስታድዬም ህዳር ሰባት ለሚያደርጉት ፍልሚያ ዝግጅቱን ትናንት ጀምረዋል፡፡ በመልሱ ጨዋታ ናይጀሪያ ለ5ኛ ጊዜ ለዓለም ዋንጫ ለመብቃት ስታነጣጥር ኢትዮጵያ ምስራቅ አፍሪካን በመወከል የመጀመሪያ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ማግኘቱን ታልማለች፡፡

ናይጄርያ በአዲስ አበባ በተደረገው የመጀመርያ ጨዋታ ኢትዮጵያን 2ለ1 ካሸነፈች በኋላ የማለፍ እድሏን እንዳመቻቸች ሲገለፅ፤ በሌላ በኩል በኳስ ቁጥጥር እና በጨዋታ ናይጄርያ ላይ ብልጫ ማሳየቱ የተነገረላት ኢትዮጵያ የማለፍ ተስፋዋን ከሜዳው ውጭ የምተወስንበት አጣብቂኝ ውስጥ ገብታለች። ናይጄርያ ኢትዮጵያን 2ለ1 ካደረገች በኋላ በዓለም ዋንጫ ማጣርያ 27ኛ ግጥሚያዋን በማሸነፍ በአፍሪካ ደረጃ በብዙ ጨዋታዎች ያለመሸነፍ ክብረወሰን ሆኖላታል፡፡ ናይጄርያ በካላባር በምታደርገው ጨዋታ ተሸንፋ አለማወቋ በመልሱ ትንቅንቅ የኢትዮጵያን ፈተና ያከብደዋል፡፡ የእግር ኳስ ዘጋቢው ድረገፅ ጎል ዶት ኮም በመልሱ ጨዋታ ማን ያሸንፋል በሚል ጥያቄ አንባቢዎቹን አሳትፎ በሰራው የውጤት ትንበያ አሸናፊነቱ 76.2 በመቶ ለናይጄርያ 23.8 በመቶ ለኢትዮጵያ ግምት ተሰጥቷል፡፡ 3ለ0 ፤ 1ለ0 እና 3ለ1 ናይጄርያ እንደምታሸንፍ የጎል አንባቢዎች ተንብየዋል፡፡

አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በመልሱ ጨዋታ የማሸነፍ እድል መኖሩን ተናግረዋል፡፡ በመጀመርያው ጨዋታ እንዳሳየነው የኳስ ብልጫ ናይጄርያን በሜዳው ስንገጥም ከፍተኛ ትግል አድርገን 2-0 አልያም 2-1 ማሸነፍ እንችላለንም ብለዋል፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በቀሪው 1ወር በሚኖራቸው ዝግጅት የወዳጅነት ጨዋታ እንደሚያስፈልጋቸው ያስታወቁ ሲሆን ለቡድኑ የማለፍ እድል ቀላል ግምት መሰጠት እንደሌለበት በማሳሰብ ከትልቅ ቡድን ጋር የአቋም መፈተሻው እንዲዘጋጅላቸው ሃሳባቸውን ገልፀዋል፡፡ አሰልጣኝ ስቴፈን ኬሺ በበኩሉ በተገኘው ድል የተሰማውን ደስታ በገለፀበት ወቅት ‹‹ያሸነፍነው እልህ አስጨራሽ ትግል በማድረግ ነው፡፡ በተለይ በጨዋታው ያደረግኳቸው ሁለት ቅያሪዎች ግጥሚያውን ወደራሳችን አጨዋወት በመቀየር ድላችንን ለማረጋገጥ ምክንያት ሆኖልናል፡፡›› በማለት ተናግሯል፡፡ ስቴፈን ኬሺ ለመልሱ ጨዋታ አዲስ እቅድ በመንደፍ እንሰራለን ብሎ በተናገረበት ወቅት ናይጄርያውያን ከኢትዮጵያን ድጋፍ አሰጣጥ ተምረው በካላባር በሚደረገው ጨዋታ ስታድዬሙን በነጭ እና አረንጓዴ ቀለሞች በማሸብረቅ እንዲደግፉ ጥሩ አቅርቧል፡፡

ናይጄርያ ከኢትዮጵያ ጋር ከምታደርገው ጨዋታ በፊት ከዮርዳኖስ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ታደርጋለች፡፡ ከመልሱ ጨዋታ ሁለት ቀናት በኋላ ደግሞ በለንደን ከተማ በሚገኘው የፉልሃም ክለብ ስታድዬም ክራቫን ኮቴጅ ከአራት ጊዜ የዓለም ሻምፒዮኗ ጣሊያን ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ እቅድ ይዛለች፡፡ ይህን የወዳጅነት ጨዋታ የናይጄርያ የእግር ኳስ ፌደሬሽን ያዘጋጀው በዓለም ዋንጫ ከሚያደርገው ዝግጅት ጋር በተያያዘ 2013 ከመገባደዱ በፊት ከዓለም አስር ምርጥ ቡድኖች ከአንዱ ጋር ንስሮቹ መጫወት እንዳለባቸው አቅዶ ሲሰራ በመቆየቱ ነው፡፡ የጨዋታ ብልጫ፤ የዳኝነት በደልና መረብ ያልነኩት ኳሶች

በዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ከሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ስታድዬም ኢትዮጵያ ከናይጄርያ የተገናኙበት የመጀመርያ ጨዋታ በአፍሪካ ዞን ከተደረጉ ሌሎች 4 ጨዋታዎች አነጋጋሪው ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጀመሪያው ግማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ አስደናቂ አጨዋወት በማሳየት ናይጄርያን በከፍተኛ ደረጃ አጨናንቆ ነበር፡፡ ዋልያዎቹ በመጀመርያዎቹ 15 ደቂቃዎች ከሶስት በላይ ጎል የማግባት እንቅስቃሴዎች በናይጄርያ የግብ ክልል አድርገዋል በአጨራረስ ድክመት ከመረብ ለማዋሃድ አልሆነላቸውም፡፡ በ23ኛው ደቂቃ ላይ ሳላዲን ሰይድ ከመሃል የተሻገረለትን ኳስ የናይጄሪያ ተከላካዮችን አታልሎ በማለፍ ወደ ግብ መታ፡፡ ኳሷ የናይጄርያውን ግብ ጠባቂ

ኢትዮጵያ በዓለም ዋንጫ ዋዜማ ላይ!?

ኢኒዬማ አምልጣ የግቡን መስመር ብታልፍም የናይጄሪያ ተከላካይ ከጐል ውስጥ አወጣት፡፡ በዚያች ቅፅበት ሳላዲን ሰይድ ደስታውን እየገለፀ ነበር፡፡ ካሜሮናውያኑ የመስመር እና የመሃል ዳኞች ግን ተነጋግረው ጎሏን ሳያፀድቋት ቀሩ። ይህች የግብ አጋጣሚ መበላሸቷ የዋልያዎቹን በማጥቃት ላይ የተመሰረተ አጨዋወት እና በስታድዬም የነበረውን ደጋፊ ስሜት አዘበራረቀ፡፡ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የተደረገው አስደንጋጭ ሙከራ በሳላዲን ሰይድ ነበር፡፡ በግራ መስመር ወደ ግብ የመታትን ኳስ ኢኒዬማ በአስደናቂ ብቃት አድኗታል፡፡ በሁለተኛው አጋማሽ ዋልያዎቹ በማጥቃት ጨዋታቸው በናይጄሪያ ቡድን ላይ ተደጋጋሚ ጫናዎችን በመፍጠር ቀጠሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይም በ57ኛው ደቂቃ ላይ በሃይሉ አሰፋ በግራ መስመር ናይጄርያ ክልል ውስጥ ገብቶ ኳሷን ወደ ግብ ክልል አሻገራት። የናይጄሪያው ግብ ጠባቂ ቪንሰንት ኢኒዬማ ኳሷን ሲይዛት የግብ መስመሩን በሙሉ ሰውነቱ አልፎ ገብቶ ነበር፡፡ ይህን ተከትሎ የመስመር ዳኛው ጎሏ እንደገባች በማሳወቃቸው ወዲያወኑ የመሃል ዳኛው ግቧን በማፅደቅ ኢትዮጵያ 1ለ0 መምራት ጀመረች፡፡ ጎሏ በስታድዬም የነበረውን ደጋፊ ከማነቃቃቷም በላይ በናይጄርያ ቡድን አቋም ላይ መሸበርን የፈጠረች ነበረች፡፡ ከዚህ በኋላ ግን ማንም ባልጠበቀው ውሳኔያቸው አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው የዋልያዎቹን አጨዋወት የሚያውክ የተጨዋች ቅያሪ አደረጉ። በመሃል ሜዳ ላይ ጥሩ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የቆየውን አዳነ ግርማን በአጥቂው ኡመድ ኡክሪ ቀየሩት፡፡ተጨማሪ ጐል ዋልያዎቹ እንዲያገቡ ከመፈለግ አንፃር ነበረ፡፡ ይህ የተጨዋች ለውጥ በብሄራዊ ቡድኑ አጨዋወት ላይ የፈጠረው ተፅእኖ ቀላል አልነበረም፡፡ ከአዳነ መውጣት በኋላ አሰልጣኝ ስቴፈን ኬሺ የመሃል ሜዳውን ለመቆጣጠር ሁለት ተጫዋቾች በአስር ደቂቃዎች ልዩነት ቀይሮ አስገባ፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይም በ67ኛው ደቂቃ ላይ ኢማኑዌል ኤሚኒኬ ከመሀል ጀምር ኳስ በመግፋት ከፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውጪ ወደግብ አክርሮ መታ፡፡ ድንገተኛዋን ኳስ ያልጠበቀው ጀማል ጣሰው ሊያድናት የቻለውን ያህል ቢወረወርም ናይጄሪያውያን አቻ ያደረገች ጎል ሆነች፡፡ ጨዋታው 1 እኩል በሆነ አቻ ውጤት ቀጠለ፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት በአዳነ ቅያሪ የሳሳውን አማካይ መስመር ለማስተካከል በሚመስል ውሳኔ ሽመልስ በቀለን በማስወጣት አዲስ ህንፃ እንዲቀየር አደረጉ፡፡ ይሁንና ይህ ቅያሬ ናይጄርያውያን ጨዋታውን አሸንፎ ለመውጣት የጀመሩትን የተጠናከረ እንቅስቃሴ የመገደብ አቅም አልነበረውም፡፡ ጨዋታው ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩት ኢማኑዌል ኢሚኒኬ ተከላካዩን አይናለም ሃይሉን በማለፍ ወደ ፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውስጥ ገባ፡፡ አይናለም ያመለጠው ኢሚኒኬን ማልያ ጎትቶ በማስቀረቱ ዳኛው የፍጹም ቅጣት ምት ለናይጄሪያ ሰጡ፡፡ ወዲያውኑ ኢማኑዌል ኢሚኒኬ ለራሱና ለቡድኑ ሁለተኛውን ጐል በቀላሉ ለማስቆጠር ችሏል።

ከኢትዮጵያና ናይጄሪያ ጨዋታ ማግስት በተለያዩ የመገናኛ ብዙሐናት የዋልያዎቹ አጨዋወት ቢደነቅም በግብ ክልል ወሳኝ የጐል አጋጣሚዎችን በመፍጠር ቡድኑ የተዳከመ መሆኑ ለሽንፈት ምክንያት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ዋልያዎቹ ማራኪ የኳስ ቅብብልና ቁጥጥር በማሳየት የአፍሪካ ሻምፒዮን የሆኑትን ንስሮቹን ማስጨነቃቸው እና ከተለያዩ የአውሮፓ ክለቦች ምርጥ ተጫዋቾች የተሰባሰቡበትን የናይጄርያቡድን በመግጠም ልዩ ብቃት ማሳየታቸው ስፖርት አፍቃሪ የገጠመውን ሽንፈት በፀጋ እንዲቀበል ያስቻለ ነበር፡፡ የሱፕር ስፖርት ዘጋቢ ስለጨዋታው ባሰፈረው ትንተና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በአጨዋወታቸው በኳስ ቁጥጥር ተሽለው ቢታዩም ለጎል የሚበቁ የመጨረሻ ኳሶችን በማቀበል ውጤታማ እንዳልነበሩና ይህን ውጤት አልባ እና ተረከዝ የበዛበት የኳስ ቅብብል ለሰርከስ ካልሆነ ውጤት ለሚያስፈልገው ወሳኝ ግጥሚያ ማድረጋቸውን አሰልጣኙ ማረም ነበረባቸው ብሏል፡፡ በአዲስ አበባው ጨዋታ ኢትዮጵያውያን ደጋፊዎች ቡድናቸው በሜዳው ሁለት ለአንድ መመራት ጀምሮ የጨዋታው ክፍለ ጊዜ ሊጠናቀቅ 23 ደቂቃዎች እየቀሩ ሊያበረታታ ከሚችል ድጋፍ

መቆጠባቸው እንዳሳፈረው በትንተናው የገለፀው ዘጋቢው በስታድዬሙ ከ35ሺ የዋልያዎቹ ደጋፊዎች ይልቅ በመቶዎች የሚቆጠሩት ናይጄርያውያን ጩሀት ጎልቶ መሰማቱን እንደታዘበ አብራርቷል፡፡

የናይጄርያ የስፖርት ሚኒስትር ንስሮቹ የሚገባቸውን ድል እንዳስመዘገቡ የተናገሩት እንደአፍሪካ ሻምፒዮን ተጫውተው የመጀመርያውን ምእራፍ እንደዘጉ በማስገንዘብ ነው፡፡ በአዲስ አበባ ለአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ተገኝተው የነበሩት ፕሬዝዳንት ጉድላክ ጆናታን ቡድናቸውን ከጨዋታ በፊት በመጎብኘት ማበረታቻ ማድረጋቸውንም አመስግነዋል። በናይጄርያ ብሄራዊ ቡድን ምክትል አሰልጣኝ የነበሩት ፋቲ አማዎ ንስሮቹ ለመልሱ ጨዋታ እንዳይዘናጉ አስጠንቅቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቡድን ያልተጠበቀ ድል የማስመዝገብ አቅም እንደሚኖራቸው በማሳሰብም ለዓለም ዋንጫ የመድረስ እድላችው ገና 75 በመቶ የተረጋገጠ በመሆኑ ለሚቀረው የ90 ደቂቃ ጨዋታ አቻ ለመውጣት ወይም ለማሸነፍ ታስቦ መሰራት አለበት የሚል ምክራቸውን ለግሰዋል፡፡ ሌላው የቀድሞ የናይጄርያ ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ኦገስቲን ኢግዌቨን እንደተናገረው ደግሞ ናይጄርያውያን የአዲስ አበባውን ጨዋታ ድል ሊያደርጉ የቻሉት ባላቸው ልምድ ከኢትዮጵያ የተሻሉ ሆነው በመገኘታቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያውያኑ በኳስ ቁጥጥር የላቁ እንደነበሩ የመሰከረው ኢግዌቨን በመልሱ ጨዋታ ንስሮቹ ሃላፊነታቸውን አሳክተው መጨረሳቸውን እጠብቃለሁ ብሏል፡፡

ከዋልያዎቹ አስደናቂ አጨዋወት ባሻገር በከፍተኛ ደረጃ ያነጋገረው በካሜሮናዊው ዳኛ የተሻረው የሳላሃዲን ሰኢድ ግብ ነበር፡፡ በጨዋታው ማግስት ይህ ጎል ፀድቋል ተብሎ ግራ መጋባት ተፈጥሮ ነበር፡፡ ሰኞ አመሻሹ ላይ ኢትዮጵያ አቻ ሆናለች በሚል የተናፈሰው መረጃ ሃሰት ነበር። መስመሩን እንዳለፈች በብዙ ዘገባዎች የተወራላት ጎል ትክክለኛ ብትሆን እንኳን ጎሏን ያላፀደቀው ዳኛው መቀጣቱ እንጂ ጎሉ የሚፀድቅበት ሁኔታ አልነበረም ፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ይህን በተመለከተ የክስ ማመልከቻውን ለአለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ፊፋ አቅርቦም ነበር። ፈፋ ለፌደሬሽኑ በላከው ምላሽ በመተዳደሪያ ህጉ አንቀፅ በመጥቀስ ክሱን ተቀባይነት እንደሌለው አሳውቋል፡፡ ቪንሰንት ኢኒዬማ ለኢትዮጵያ የተመዘገበችው የመጀመርያ ጐል ብዙዎች እንደሚያስቡት የግብ መስመሩን አላለፈችም ብሎ በልበሙሉነት የተናገረው በጨዋታው ማግስት ነው። “እንደ እኔ አቋም ግብ አልነበረችም፡፡ ለምን እንደተሰጠ አላውቅም፡፡ ኳሷን የያዝኳት መስመሩን አልፋ አይደለም። የመስመር ዳኛው እንዴት ጐሉን እንዳፀደቀ መረዳት አልቻልኩም” ሲልም አስተያየት ሰጥቷል፡፡ ኢትዮጵያ ተሽሮበታል ስለተባለችው መረብ ያልነካች ኳስ አስተያየቱን ሊሰጥ ደግሞ “በእኔ እይታ ጐል አልገባችም፡፡ በተለያየ አንግል የሚቀርፁ ካሜራዎች የተለያዩ ምስሎችን ሊያመለክቱ ይችላሉ፡፡ የግብ መስመር ቴክኖሎጂ አስፈላጊነት እዚህ ላይ ነው፡፡›› ብሎ ተናግሯል፡፡ ሌላው የውዝግብ አጀንዳ ደግሞ የናይጄሪያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በኢትዮጵያ ደጋፊዎች ድንጋይ ውርወራ ጉዳት እንደደረሰ በመግለፅ ፊፋ እርምጃ እንዲወስድ መክሰሱ ነው፡፡ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ለዚሁ ክስ እስከትናንት በስቲያ ምላሽ አልሰጠም፡፡

ለ20ኛው የዓለም ዋንጫ 18 ደርሰዋል፤ 14 ይቀራሉ፡፡ ባለፈው ሰሞን በ20ኛው የዓለም ዋንጫ አፍሪካን

በመወከል የሚሳተፉ 5 ቡድኖች ለመለየት በተደረጉት የጥሎ ማለፍ የመጀመርያ ዙር ጨዋታዎች በኋላ አልጀሪያ፣ ካሜሮን፣ አይቬሪኮስት፣ ናይጄሪያና ጋና በመልስ ጨዋታቸው ወደ ዓለም ዋንጫ የሚያልፉበትን የተሻለ ዕድል ይዘዋል፡፡ ከዓለም ዋንጫው የጥሎ ማለፍ ትንቅንቆች ኢትዮጵያ በሜዳዋ ናይጀሪያ አስተናግዳ 2ለ1 ከተሸነፈችበት ጨዋታ ባሻገር፣ አይቬሪኮስት ሴኔጋልን 3ለ1፤ ቡርኪናፋሶ አልጀሪያን 3ለ2 እንዲሁም ጋና ግብጽን 6ለ1 በሆነ ውጤት በየሜዳቸው አሸንፈዋል፡፡ ቱኒዚያ ደግሞ በሜዳዋ ካሜሮንን አስተናግዳ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡ ከወር በኋላ በሚደረጉት የመልስ ጨዋታዎች ከ4 ዓመት በፊት ደቡብ አፍሪካ ባስተናገደችው 19ኛው ዓለም ዋንጫ አፍሪካን የወከሉት ቡድኖች በብራዚሉ 20ኛው ዓለም ዋንጫ ላይ ውክልናቸውን እንደሚደግሙ ግምት አሳድሯል፡፡ እነሱም አልጀሪያ፣ ካሜሮን፣ አይቬሪኮስት፣ ናይጄሪያና ጋና ናቸው። ከአፍሪካ ባሻገር ባለፈው ሳምንት በመላው ዓለም ከተካሄዱ ሌሎች የዓለም ዋንጫ የማጣሪያ ውድድሮች በኋላ ለ20ኛው የዓለም ዋንጫ ያለፉት ብሔራዊ ቡድኖች ብዛት 18 ደርሷል፡፡ ከ1 ወር በኋላ በቀሩት የ14 ብሔራዊ ቡድን ኮታዎች ተሳትፏቸውን የሚያረጋግጡ ብሄራዊ ቡድኖች ተለይተው ይታወቃሉ፡፡ ከአውሮፓ ዞን ያለፉት 9 አገራት ሆላንድ፣ ጣልያን፣ ቤልጅየም፣ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ስፔን፣ እንግሊዝ፣ ሩስያ እና ቦስኒያ ሄርዞጐቪና ናቸው፡፡ ለአውሮፓ በሚቀሩት የአራት ቡድኖች ኮታዎች ፖርቱጋል፣ ክሮሽያ፣ ዩክሬን፣ ግሪክ፣ ፈረንሳይ፣ ስዊድን፣ ሮማንያ እና አይስላንድ በጥሎ ማለፍ የመጨረሻ ትንቅንቅ የሚደረግላቸውን የጨዋታ ድልድል በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡ ከኤሽያ ዞን ለዓለም ዋንጫው ማለፋቸውን ያረጋገጡት አራት አገራት ጃፓን፣ አውስትራሊያ፣ ኢራንና ደቡብ ኮርያ ናቸው፡፡ በሚቀረው የአንድ ብሔራዊ ቡድን ኮታ ከኤሽያ ዞን የምትወከለው ዮርዳኖስ እና የደቡብ አሜሪካ ተወካይ የሆነችው ኡራጋይ በጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ይገናኛሉ፡፡ ከደቡብ አሜሪካ ዞን አዘጋጇን ብራዚል ጨምሮ አርጀንቲና ፣ ኮሎምቢያ ቺሊና ኢኳዶር ማለፋቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ከሰሜንና መካከለኛው አሜሪካ ዞን አሜሪካ፣ ኮስታሪካና ሆንዱራስ ማለፋቸውን ሲያረጋግጡ በቀረው የአንድ ብሔራዊ ቡድን ኮታ ከዚሁ ዞን የምትወከለው ሜክሲኮና ከኦሽንያ የምትወከለው ኒውዝላንድ በጥሎ ማለፍ ይተናነቁበታል፡፡

አዲሱ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ጁነዲን ባሻ

‹‹እግር ኳስ ከዝንባሌ ባሻገር

ትልቅ ንግድ ነው››

Page 28: Issue 718

Website: www.addisadmassnews.com

አዲስ አድማስ ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ገፅ 28 ማ

ስታ

ወቂ